Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ከዚ​ህም በኋላ ሩፋ​ኤል ጦብ​ያን አለው፥ “አንተ ወን​ድሜ አባ​ት​ህን እን​ዴት እንደ ተው​ኸው አታ​ው​ቅ​ምን?

2 ና ከሚ​ስ​ትህ ቀድ​መን ሄደን ቤቱን እና​ዘ​ጋጅ።

3 የዚ​ህ​ንም ዓሣ ሐሞት ያዝ፤” ያም ከእ​ነ​ርሱ ጋር የተ​ከ​ተ​ለው ብላ​ቴና ከእ​ነ​ርሱ ጋር ሄደ።

4 ሐና ግን በጎ​ዳና ተቀ​ምጣ ልጅ​ዋን ታይ ዘንድ ትመ​ለ​ከት ነበር።

5 ሲመ​ጣም አየ​ችው፤ ሄዳም አባ​ቱን፥ “እነሆ፥ ልጅህ መጣ፤ ከእ​ር​ሱም ጋር የሄ​ደው ያ ሰው መጣ” አለ​ችው።


የጦ​ቢት ዐይን እንደ በራ

6 ሩፋ​ኤ​ልም አለው፥ “ያባ​ትህ ዐይ​ኖች እን​ዲ​በሩ አው​ቃ​ለሁ፤

7 አንተ ግን ያን ሐሞት ያባ​ት​ህን ዐይን ኳለው፤ በተ​ኳ​ለም ጊዜ ዐይ​ኖ​ቹን ያሻል፤ ብል​ዙም ከዐ​ይኑ ይወ​ጣል፤ በደ​ኅ​ናም ያያል።”

8 ሐናም ሮጣ የል​ጅ​ዋን አን​ገት አቅፋ፥ “ልጄ ሆይ፥ ካየ​ሁህ እን​ግ​ዲህ ልሙት” አለ​ችው፤ ሁለ​ቱም አለ​ቀሱ።

9 ጦቢ​ትም ወደ ደጅ ወጣ፤ ተሰ​ነ​ካ​ከ​ለም፤ ልጁም ሮጦ አባ​ቱን አነ​ሣው።

10 የአ​ባ​ቱ​ንም ዐይ​ኖች በዚያ ሐሞት ኳለና፥ “አባቴ ሆይ፥ እን​ደ​ም​ት​ድን ታመን” አለው።

11 በኳ​ለ​ውም ጊዜ ዐይ​ኖ​ቹን አሸ።

12 ብል​ዙም ከዐ​ይኑ ብሌን ተገ​ፈፈ፤ ልጁ​ንም አየው፤ አን​ገ​ቱ​ንም አቅፎ አለ​ቀሰ።

13 እን​ዲ​ህም አለ፥ “ጌታ ሆይ፥ የተ​መ​ሰ​ገ​ንህ ነህ፤ ስም​ህም ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ይመ​ስ​ገን፤ ቅዱ​ሳን መላ​እ​ክ​ት​ህም ሁሉ ቡሩ​ካን ናቸው፤ ገር​ፈህ ይቅር ብለ​ኸ​ኛ​ልና።

14 እነ​ሆም፥ ልጄ ጦብ​ያን አየ​ሁት፤” ከዚ​ህም በኋላ ልጁ ደስ እያ​ለው ገባ፤ ለአ​ባ​ቱም በሜ​ዶን የተ​ደ​ረ​ገ​ለ​ትን ታላ​ላቅ ነገር ሁሉ ነገ​ረው።

15 ጦቢ​ትም ደስ እያ​ለው ወጥቶ ምራ​ቱን ተቀ​በ​ላት፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም በነ​ነዌ አደ​ባ​ባይ አመ​ሰ​ገ​ነው፤ ሲሄ​ድም ያዩት ሰዎች፥ “እን​ዴት አየ?” ብለው አደ​ነ​ቁት።

16 ጦቢት ግን በፊ​ታ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ገነ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይቅር ብሎ​ታ​ልና። ጦቢ​ትም ወደ ምራቱ ወደ ሣራ በደ​ረሰ ጊዜ፥ “ልጄ! እን​ኳን በደ​ኅና ገባሽ!” ብሎ መረ​ቃት፤ ወደ እኛ ያመ​ጣሽ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ይመ​ስ​ገን፤ አባ​ት​ሽ​ንና እና​ት​ሽ​ንም ይባ​ርክ” አላት። በነ​ነ​ዌም ለሚ​ኖሩ ለወ​ን​ድ​ሞቹ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ።

17 አኪ​አ​ክ​ሮ​ስም መጣ፤ የወ​ን​ድሙ ልጅ ነሳ​ቦ​ስም መጣ።

18 ሰባት ቀንም በደ​ስታ የሰ​ርግ በዐል አደ​ረጉ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች