የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

ማስታወቂያዎች


መላው መጽሐፍ ቅዱስ ብሉይ ኪዳን አዲስ ኪዳን




መጽ​ሐፈ ጦቢት 14:10 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እናትህን እኔ አጠገብ እንደቀበርካት ቀኑ መቼም ይሁን መቼ በዚያኑ ቀን ሂድ፤ ክፋትና፥ ሸፍጥ ያለ ሃፍረት አሸንፎ በማይባት በዚች ከተማ ውስጥ አትቆይ። ልጄ ሆይ በአሳዳጊ አባቱ በአሂካር ላይ ናዳብ ያደረገውን ተመልከት፤ አሂካር በሕይወት እያለ ወደ ጉድጓድ እንዲገባ አልተደረገምን? እግዚአብሔር ግን የጭካኔ ሥራውን በተበዳዩ ዐይን ፊት እንዲከፍል አድርጎታል። ናዳብ አሂካርን ለመግደል ስለፈለገ ተቀጥቶ ወደ ዘለዓለም ጨለማ ወረደ፥ አሂካር ግን ወደ ብርሃን ወጣ፤ በደግ ሥራው ምክንያት አሂካር ናዳብ ካጠመደበት ከሞት ወጥመድ ወጣ፥ ናዳብ ግን ወደ እራሱ ወጥመድ ወደቀ።

ምዕራፉን ተመልከት

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

አክ​ብ​ረህ ቅበ​ረኝ፤ እና​ት​ህ​ንም ከእኔ ጋር ቅበ​ራት። ልጄ፥ በነ​ነዌ አት​ቈይ። ሐማ በዘ​መ​ድህ በአ​ኪ​አ​ክ​ሮስ ያደ​ረ​ገ​ውን፥ ከብ​ር​ሃን ወደ ጨለማ እን​ዳ​ገ​ባው፥ ፍዳ​ው​ንም እንደ ተቀ​በለ፥ አኪ​አ​ክ​ሮ​ስም እንደ ዳነ እይ። እርሱ ግን ፍዳ​ውን ተቀ​በለ፤ እርሱ ወደ ጨለማ ወረደ። ምናሴ ምጽ​ዋ​ትን አደ​ረገ፤ እው​ነ​ት​ንም አደ​ረገ፤ ከመ​ከ​ሩ​በት ከሞት መቅ​ሠ​ፍ​ትም ዳነ። ሐማ ግን በዚ​ያች ወጥ​መድ ወደ​ቀና ሞተ።

ምዕራፉን ተመልከት



መጽ​ሐፈ ጦቢት 14:10
0 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች