ሶስተኛውን አሥራት ለሙት ልጆች፥ ለመበለቶችና ከእሥራኤል ልጆች ጋር ለሚኖሩ እንግዶች እሰጥ ነበር፤ በየሶስት ዓመቱ እንደ ስጦታ እሰጣቸው ነበር፤ ስንበላም በሙሴ ሕግ ለተደነገገውና ለአያታችን ለአናኒኤል እናት ምክር እንታዘዝ ነበር፥ እኔ አባቴ ሞቶብኝ የሙት ልጅ ነበርሁና።
ሦስተኛውንም እጅ ዐሥራት የአባቴ እናት ዲቦራ እንዳዘዘች ለድሆች እሰጥ ነበር። አባቴና እናቴ በድኃአደግነት ትተውኛልና፤