Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 67 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ የዳ​ዊት የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር።

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይነሣ፥ ጠላ​ቶ​ቹም ይበ​ተኑ፥ የሚ​ጠ​ሉ​ትም ከፊቱ ይሽሹ።

2 ጢስ እን​ደ​ሚ​በ​ንን እን​ዲሁ ይብ​ነኑ፤ ሰም በእ​ሳት ፊት እን​ደ​ሚ​ቀ​ልጥ፥ እን​ዲሁ ኃጥ​ኣን ከአ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ይጥፉ።

3 ጻድ​ቃን ግን ደስ ይበ​ላ​ቸው፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ሐሤ​ትን ያድ​ርጉ፥ በደ​ስ​ታም ደስ ይበ​ላ​ቸው።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግኑ፤ ለስ​ሙም ዘምሩ፤ ወደ ምዕ​ራብ ለወ​ጣው መን​ገ​ድን አብጁ፤ ስሙ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፥ በፊ​ቱም ደስ ይበ​ላ​ችሁ፤ ከፊ​ቱም የተ​ነሣ ይደ​ነ​ግ​ጣሉ።

5 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቅ​ዱስ ቦታው ለድሃ አደ​ጎች አባት፥ ለባ​ል​ቴ​ቶ​ችም ዳኛ ነው።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብቸ​ኞ​ችን በቤቱ ያሳ​ድ​ራ​ቸ​ዋል፥ እስ​ረ​ኞ​ች​ንም በኀ​ይሉ ያወ​ጣ​ቸ​ዋል፤ በመ​ቃ​ብር የሚ​ኖሩ ኀዘ​ን​ተ​ኞ​ች​ንም እን​ዲሁ።

7 አቤቱ፥ በሕ​ዝ​ብህ ፊት በወ​ጣህ ጊዜ፥ በም​ድረ በዳም ባለ​ፍህ ጊዜ፥

8 ከሲና አም​ላክ ፊት፥ ከእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ፊት ምድር ተና​ወ​ጠች፥ ሰማ​ያ​ትም አን​ጠ​ባ​ጠቡ።

9 አቤቱ፥ በፈ​ቃ​ድህ ዝና​ብን ለር​ስ​ትህ ለየህ፥ በደ​ከ​መም ጊዜ አንተ ታጸ​ና​ዋ​ለህ።

10 እን​ስ​ሶ​ችህ በው​ስጡ ያድ​ራሉ፤ አቤቱ፥ በቸ​ር​ነ​ትህ ለድ​ሆች አዘ​ጋ​ጀህ።

11 ብዙ ኀይ​ልን ለሚ​ያ​ወሩ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃሉን ሰጠ፤

12 ለኀ​ያ​ላን ንጉሥ ለወ​ዳጁ፤ ለወ​ዳ​ጁና ለቤ​ትህ ውበት ምር​ኮን ተካ​ፈ​ልን።

13 በር​ስ​ቶች መካ​ከል ብታ​ድሩ፥ ከብር እንደ ተሠሩ እንደ ርግብ ክን​ፎች፥ በቅ​ጠ​ልያ ወር​ቅም እንደ ተለ​በጡ ላባ​ዎ​ችዋ ትሆ​ና​ላ​ችሁ።

14 ሰማ​ያዊ ንጉሥ በላ​ይዋ ባዘዘ ጊዜ፥ በሰ​ል​ሞን ላይ በረዶ ይዘ​ን​ማል።

15 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተራራ የለ​መ​ለመ ተራራ ነው፤ የጸና ተራ​ራና የለ​መ​ለመ ተራራ ነው።

16 የጸኑ ተራ​ራ​ዎች ለምን ይነ​ሣሉ? እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያድ​ር​በት ዘንድ የወ​ደ​ደው ተራራ ይህ ነው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያድ​ር​ባ​ቸ​ዋ​ልና።

17 የብዙ ብዙ ሺህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰረ​ገ​ላ​ዎች ደስ​ተ​ኞች ናቸው። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በመ​ቅ​ደሱ በሲና በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ነው።

18 ምር​ኮን ማር​ከህ ወደ ሰማይ ወጣህ ስጦ​ታ​ህ​ንም ለሰ​ዎች ሰጠህ፥ ያድሩ ዘንድ ይክዱ ነበ​ርና።

19 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላክ ቡሩክ ነው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በየ​ዕ​ለቱ ቡሩክ ነው፤ አም​ላ​ካ​ች​ንና መድ​ኃ​ኒ​ታ​ችን ይረ​ዳ​ናል።

20 አም​ላ​ካ​ች​ንስ የማ​ዳን አም​ላክ ነው፤ የሞት መን​ገድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው።

21 ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የጠ​ላ​ቶ​ቹን ራስ ይሰ​ብ​ራል፥ በጠ​ጉ​ራ​ቸው ጫፍም በደ​ላ​ቸው ይሄ​ዳል።

22 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ አለ፦ ወጥቼ እመ​ለ​ሳ​ለሁ፥ በባ​ሕ​ሩም ጥልቅ እመ​ለ​ሳ​ለሁ፥

23 እግ​ሮ​ችህ በደም ይነ​ከሩ ዘንድ፥ የው​ሾ​ችህ ምላስ በጠ​ላ​ቶ​ችህ ላይ ነው።

24 አቤቱ፥ መን​ገ​ድህ ተገ​ለጠ። የአ​ም​ላ​ካ​ችን የን​ጉሡ መን​ገድ በመ​ቅ​ደሱ

25 አለ​ቆች ደረሱ፥ መዘ​ም​ራ​ንም አሏ​ቸው ከበ​ሮን በሚ​መቱ በደ​ና​ግል መካ​ከል።

26 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በጉ​ባኤ፥ አም​ላ​ካ​ች​ን​ንም በእ​ስ​ራ​ኤል ምን​ጮች አመ​ሰ​ገ​ኑት።

27 ወጣቱ ብን​ያም በጉ​ል​በቱ በዚያ አለ፥ ገዦ​ቻ​ቸው የይ​ሁዳ አለ​ቆች፥ የዛ​ብ​ሎን አለ​ቆ​ችና የን​ፍ​ታ​ሌ​ምም አለ​ቆች።

28 አቤቱ፥ በኀ​ይ​ልህ እዘዝ፤ አቤቱ፥ ይህን ለእኛ የሠ​ራ​ኸ​ውን አጽ​ናው።

29 በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለው መቅ​ደ​ስህ ነገ​ሥ​ታት እጅ መን​ሻን ለአ​ንተ ያመ​ጣሉ።

30 በቀ​ር​ካሃ ውስጥ ያሉ​ትን አራ​ዊት፥ በሕ​ዝብ ጊደ​ሮች መካ​ከል የበ​ሬ​ዎ​ችን ጉባኤ ገሥጽ፥ እንደ ብር የተ​ፈ​ተ​ኑት አሕ​ዛብ እን​ዳ​ይ​ዘጉ፤ ሰል​ፍን የሚ​ወ​ድ​ዱ​ትን አሕ​ዛ​ብን በት​ና​ቸው።

31 መል​እ​ክ​ተ​ኞች ከግ​ብፅ ይምጡ፤ ኢት​ዮ​ጵያ እጆ​ች​ዋን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትዘ​ረ​ጋ​ለች።

32 የም​ድር ነገ​ሥ​ታት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት፥ ለአ​ም​ላ​ካ​ች​ንም ዘምሩ።

33 በም​ሥ​ራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማ​ያት ለወጣ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘምሩ፤ የኀ​ይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰ​ጣል።

34 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋ​ናን ስጡ፤ ግር​ማው በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ፥ ኀይ​ሉም እስከ ደመ​ናት ነው።

35 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቅ​ዱ​ሳኑ ላይ ድንቅ ነው፤ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እርሱ ኀይ​ልን ብር​ታ​ት​ንም ለሕ​ዝቡ ይሰ​ጣል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይመ​ስ​ገን።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos