Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዕብራውያን 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ስለ ካህኑ መልከ ጼዴቅ

1 የሳ​ሌም ንጉሥ፥ የል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ካህን የሆነ፥ ይህ መልከ ጼዴቅ፥ አብ​ር​ሃም ነገ​ሥ​ታ​ትን ድል ነሥቶ በተ​መ​ለሰ ጊዜ ከእ​ርሱ ጋር ተገ​ና​ኝቶ ባረ​ከው።

2 አብ​ር​ሃ​ምም ከገ​ን​ዘቡ ሁሉ ከዐ​ሥር አንድ ሰጠው፤ መጀ​መ​ሪያ የስሙ ትር​ጓሜ የጽ​ድቅ ንጉሥ ነበር፤ በኋ​ላም የሳ​ሌም ንጉሥ ተባለ፤ የሰ​ላም ንጉሥ ማለት ነው።

3 አባት የለ​ውም፤ እና​ትም የለ​ች​ውም፤ ትው​ል​ዱም አይ​ታ​ወ​ቅም፤ ለዘ​መኑ መጀ​መ​ሪያ፥ ለሕ​ይ​ወ​ቱም መጨ​ረሻ የለ​ውም፤ ክህ​ነቱ የወ​ልደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምሳሌ ሆኖ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል።

4 የአ​ባ​ቶች አለቃ አብ​ር​ሃም ከም​ር​ኮው ሁሉ የሚ​ሻ​ለ​ውን ዐሥ​ራት የሰ​ጠ​ውን የዚ​ህን ካህን ክብር ታያ​ላ​ች​ሁን?

5 ከሌዊ ልጆ​ችም፥ ክህ​ነ​ትን የሚ​ቀ​በ​ሉት ከሕ​ዝቡ ማለት ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው፥ እነ​ርሱ ምንም ከአ​ብ​ር​ሃም ወገብ ቢወጡ ከእ​ነ​ርሱ ዐሥ​ራ​ትን በሕግ እን​ዲ​ያ​ስ​ወጡ ትእ​ዛዝ አላ​ቸው።

6 ወገ​ና​ቸው ላይ​ደለ ለእ​ርሱ ግን አብ​ር​ሃም ዐሥ​ራ​ትን ሰጠው፤ እር​ሱም ተስፋ ያለው አብ​ር​ሃ​ምን ባረ​ከው።

7 ነገር ግን ታላቁ ታና​ሹን እን​ደ​ሚ​ባ​ር​ከው ያለ ጥር​ጥር ይታ​ወ​ቃል።

8 በዚ​ህስ የሚ​ሞት ሰው ዐሥ​ራ​ትን ይቀ​በ​ላል፤ በወ​ዲ​ያው ግን ሕያው እንደ ሆነ መጽ​ሐፍ የሚ​መ​ሰ​ክ​ር​ለት እርሱ ይቀ​በ​ላል።

9 እንደ ተነ​ገ​ረም ዐሥ​ራ​ትን የሚ​ቀ​በል ሌዊ ስን​ኳን በአ​ብ​ር​ሃም በኩል ዐሥ​ራ​ትን ሰጠ።

10 መልከ ጼዴቅ በተ​ገ​ና​ኘው ጊዜ ገና በአ​ባቱ በአ​ብ​ር​ሃም ወገብ ነበ​ርና።

11 እን​ግ​ዲህ ሕዝቡ በሌዊ ክህ​ነት የተ​መ​ሠ​ረ​ተን ሕግ ተቀ​ብ​ለ​ዋ​ልና በዚያ ክህ​ነት ፍጹ​ም​ነት የተ​ገኘ ቢሆን፥ እንደ አሮን ሹመት የማ​ይ​ቈ​ጠር፥ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ግን የሆነ ሌላ ካህን ሊነሣ ወደ ፊት ስለ​ምን ያስ​ፈ​ል​ጋል?

12 ክህ​ነ​ታ​ቸው ታልፍ ዘንድ አላ​ትና፤ ክህ​ነ​ታ​ቸው ካለ​ፈ​ችም ኦሪ​ታ​ቸው ታል​ፋ​ለች።

13 ይህ ነገር የተ​ነ​ገ​ረ​ለት እርሱ በሌላ ወገን ተካ​ፍ​ሎ​አ​ልና፥ ከዚ​ያም መሠ​ዊ​ያ​ውን ያገ​ለ​ገለ ማንም የለም።

14 ጌታ​ችን ከይ​ሁዳ ነገድ እንደ ወጣ የተ​ገ​ለጠ ነውና፤ ስለ​ዚ​ህም ነገድ ሙሴ ምንም እን​ኳን ስለ ክህ​ነት አል​ተ​ና​ገ​ረም።

15 ይል​ቁ​ንም ይህ እጅግ ያስ​ረ​ዳል፤ በመ​ልከ ጼዴቅ ክህ​ነት አም​ሳል ሌላ ካህን ይነ​ሣል ብሎ​አ​ልና።

16 ይኸ​ውም በማ​ያ​ልፍ ሕይ​ወት ኀይል እንጂ ለሥ​ጋና ለደም በተ​ሠራ ሕግ አይ​ደ​ለም።

17 “እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት የዘ​ለ​ዓ​ለም ካህን አንተ ነህ” ብሎ ይመ​ሰ​ክ​ራ​ልና።

18 ስለ​ዚ​ህም የም​ት​ደ​ክም፥ የማ​ት​ጠ​ቅ​ምም ስለ ሆነች የቀ​ደ​መ​ችው ትእ​ዛዝ ተሽ​ራ​ለች።

19 ኦሪት ምንም ግዳጅ አል​ፈ​ጸ​መ​ች​ምና፤ ነገር ግን በእ​ር​ስዋ ፋንታ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የም​ን​ቀ​ር​ብ​በት ከእ​ር​ስዋ የሚ​ሻል ተስፋ ገብ​ቶ​አል።

20 እርሱ ያለ መሐላ አል​ሆ​ነም፤ ያለ መሐላ የተ​ሾሙ ካህ​ናት አሉና።

21 በመ​ሐላ የሾ​መ​ውን ግን፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማለ፥ አይ​ጸ​ጸ​ት​ምም፤ አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት የዘ​ለ​ዓ​ለም ካህን ነህ” አለው።

22 ኢየ​ሱስ ይህን ያህል በም​ት​በ​ል​ጥና ከፍ ባለች ሹመት ተሾመ።

23 ለእ​ነ​ዚ​ያስ ብዙ​ዎች ካህ​ናት ነበ​ሩ​አ​ቸው፤ ሞት ይሽ​ራ​ቸው፥ እን​ዲ​ኖ​ሩም አያ​ሰ​ና​በ​ታ​ቸ​ውም ነበ​ርና።

24 እርሱ ግን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል፤ ክህ​ነቱ አይ​ሻ​ር​ምና።

25 ዘወ​ትር በእ​ርሱ በኩል ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቀ​ር​ቡ​ትን ሊያ​ድ​ና​ቸው ይቻ​ለ​ዋል፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ሕያው ነውና ያስ​ታ​ር​ቃ​ቸ​ዋል።

26 ቅዱ​ስና ያለ ተን​ኰል፥ ነው​ርም የሌ​ለ​በት፥ ከኀ​ጢ​አ​ተ​ኞ​ችም የተ​ለየ፥ ከሰ​ማ​ያ​ትም ከፍ ከፍ ያለ፥ እን​ደ​ዚህ ያለ ሊቀ ካህ​ናት ይገ​ባ​ናል።

27 እር​ሱም እንደ እነ​ዚያ ሊቃነ ካህ​ናት አስ​ቀ​ድሞ ስለ ራሱ ኀጢ​አት በኋ​ላም ስለ ሕዝቡ ኀጢ​አት ዕለት ዕለት መሥ​ዋ​ዕ​ትን ሊያ​ቀ​ርብ አያ​ስ​ፈ​ል​ገ​ውም፤ ራሱን ባቀ​ረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድ​ር​ጎ​አ​ልና።

28 ኦሪ​ትስ የሚ​ሞት ሰውን ሊቀ ካህ​ናት አድ​ርጋ ትሾ​ማ​ለች፤ ከኦ​ሪት በኋላ የመ​ጣው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የመ​ሐላ ቃሉ ግን ዘለ​ዓ​ለም የማ​ይ​ለ​ወጥ ፍጹም ወል​ድን ካህን አድ​ርጎ ሾመ​ልን።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos