Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




1 ዜና መዋዕል 27:1 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

1 ከዚህ በታች የተመለከተው የእስራኤላውያን የቤተሰብ አለቆችና የጐሣ መሪዎች፥ እንዲሁም ዓመቱን በሙሉ በየወሩ ንጉሡንና ሕዝቡን የሚያገለግሉ የሺህ አለቆች፥ የመቶ አለቆችና አዛዦቻቸው ስም ዝርዝር ነው። እያንዳንዱ ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩት።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

1 የእስራኤል የቤተ ሰብ አለቆች፣ የሻለቆች፣ የመቶ አለቆች እንዲሁም ዓመቱን ሙሉ በየወሩ የሚመደቡትን ዋና ዋና ክፍሎች በተመለከተ ንጉሡን ያገለገሉ አለቆቻቸው ዝርዝር ይህ ነው። እያንዳንዱ ዋና ክፍል ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

1 የእስራኤልም ልጆች የአባቶች ቤቶች አለቆች የሺህ አለቆች የመቶ አለቆችም በክፍሎች ምደባ ሁሉ ንጉሡን ያገለገሉት ሹማምንት እንደ ቁጥራቸው እነዚህ ነበሩ። እነዚህም ክፍሎች እያንዳንዳቸው ሀያ አራት ሺህ ሆነው በዓመት ውስጥ ባሉት ወራት ሁሉ በየወሩ ይገቡና ይወጡ ነበር።

Ver Capítulo Copiar

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች የአ​ባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆ​ችና የሺህ አለ​ቆች፥ የመቶ አለ​ቆ​ችም ለን​ጉ​ሡና ለን​ጉሡ ትእ​ዛዝ ሁሉ የሚ​ያ​ገ​ለ​ግሉ ሹማ​ምት እንደ ቍጥ​ራ​ቸው በየ​ክ​ፍ​ላ​ቸው እነ​ዚህ ነበሩ። እነ​ዚ​ህም ክፍ​ሎች እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነው በዓ​መቱ ወራት ሁሉ በየ​ወሩ ይገ​ቡና ይወጡ ነበር።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

1 የእስራኤልም ልጆች የአባቶች ቤቶች አለቆችና የሺህ አለቆች የመቶ አለቆችም በክፍሎች ነገር ሁሉ ንጉሡን ያገለገሉትም ሹማምት እንደ ቍጥራቸው እነዚህ ነበሩ። እነዚህም ክፍሎች እያንዳንዳቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነው በዓመት ወራት ሁሉ በየወሩ ይገቡና ይወጡ ነበር።

Ver Capítulo Copiar




1 ዜና መዋዕል 27:1
18 Referencias Cruzadas  

ዝነኞች የሆኑት የዳዊት ወታደሮች ስም ዝርዝር ከዚህ በታች እንደ ተመለከተው ነው፤ የመጀመሪያው የታሕክሞን ተወላጅ ዮሼብ ባሼቤት የተባለው ሲሆን እርሱም ከሦስቱ ኀያላን ብልጫ ያለው ተቀዳሚ ነው፤ ይህ ሰው በአንድ ውጊያ ላይ ጦሩን አንሥቶ ስምንት መቶ ኀያላን ሰዎችን ገደለ።


ለሰሎሞንና በቤተ መንግሥቱ ለሚቀለቡት ሁሉ የሚያስፈልገውን ምግብ የሚያቀርቡት ዐሥራ ሁለቱ የክፍላተ ሀገር ገዢዎች እያንዳንዳቸው በተመደበላቸው ወር ምንም ነገር ሳያጓድሉ በወቅቱ ያመጡ ነበር።


ሰሎሞን በመላው እስራኤል ዐሥራ ሁለት የክፍላተ ሀገር ገዢዎችን ሾመ፤ የእነርሱም ተግባር ከየግዛታቸው ለንጉሡና ለንጉሡ ቤተሰብ ቀለብ የሚሆነውን ነገር ሁሉ ማቅረብ ነበር፤ እያንዳንዳቸውም በዓመት ውስጥ ለአንድ ወር ቀለብ የማቅረብ ግዴታ ነበረባቸው።


በእነርሱ ላይ አዶኒራም የተባለውን ሰው ኀላፊ አድርጎ ሾመ፤ ሠራተኞቹንም ዐሥር ዐሥር ሺህ አድርጎ በሦስት ቡድን በመክፈል እያንዳንዱ ቡድን ተራ ገብቶ አንድ ወር በሊባኖስ እንዲሠራ፥ ሁለት ወር ደግሞ በቤቱ እንዲያርፍ ወሰነ።


ዝነኞች የሆኑት የዳዊት ወታደሮች ስም ዝርዝር ከዚህ በታች እንደሚከተለው ነው፦ እነርሱም ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር ሆነው እግዚአብሔር በሰጠው የተስፋ ቃል መሠረት ዳዊት እንዲነግሥ በጣም ረድተዋል። መንግሥቱም ጽኑና ኀያል እንዲሆን አድርገዋል።


ንጉሥ ዳዊት የሻለቅነትና የመቶ አለቅነት ማዕርግ ካላቸው የጦር አለቆች ጋር ተመካከረ፤


ንጉሥ ዳዊት ከእነዚያ ዘመዶች መካከል ምርጥ የሆኑ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ የቤተሰብ አለቆችን መረጠ፤ ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተ ምሥራቅ ማለትም በሮቤል፥ በጋድና በምናሴ ነገድ እኩሌታ ግዛቶች መንፈሳዊውንና ዓለማዊውን ጉዳይ ሁሉ የማስተዳደር ኀላፊነት ሰጣቸው።


ለእያንዳንዱም ወር የቡድን መሪ የነበሩት ስማቸው ከዚህ በታች የተዘረዘረው ነው፦ በመጀመሪያው ወር በአንደኛው ክፍል የበላይ የሆነው የዛብዲኤል ልጅ ያሾብዓም ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ፤ እርሱም የይሁዳ ነገድ ክፍል የሆነው የፋሬስ ጐሣ አባል ነበር። በሁለተኛው ወር ክፍል ላይ የበላይ የነበረው አሖሓዊው ዶዳይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ፤ ሚቅሎትም የእርሱ ምክትል ነበር። በሦስተኛው ወር ሦስተኛው የሠራዊት አለቃ የካህኑ የዮዳሄ ልጅ በናያ ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ ይህ በናያ በሠላሳው መካከል ኀያል ሆኖ የሠላሳው አለቃ ነበረ። ልጁ ዓሚዛባድ የክፍሉ አዛዥ ነበር። በአራተኛው ወር በአራተኛው ክፍል የበላይ የሆነው የኢዮአብ ወንድም ዐሣሄል ነበር። ልጁም ዜባድያ የእርሱ ተተኪ ሆነ። በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በአምስተኛው ወር፥ በአምስተኛው ክፍል የበላይ ይጅሃራዊው ሻምሁት ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በስድስተኛው ወር፥ በስድስተኛው ክፍል የበላይ ተቆዓዊው የዒቄሽ ልጅ ዒራ ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በሰባተኛው ወር፥ በሰባተኛው ክፍል የበላይ ከኤፍሬም ነገድ ፐሎናዊ የሆነው ሔሌጽ ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በስምንተኛው ወር፥ በስምንተኛው ክፍል የበላይ የሑሻ ተወላጅ የነበረው ሲበካይ ነበር፤ እርሱም የይሁዳ ነገድ ከነበረው ከዛራ ዘር ነበር። በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በዘጠነኛው ወር፥ በዘጠነኛው ክፍል የበላይ ከብንያም ነገድ የነበረው ዓናቶታዊው አቢዔዜር ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በዐሥረኛው ወር፥ በዐሥረኛው ክፍል የበላይ ከዛራ ነገድ የነጦፋ ተወላጅ የሆነው ማሕራይ ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በዐሥራ አንደኛው ወር፥ በዐሥራ አንደኛው ክፍል የበላይ ከኤፍሬም ተወላጅ ነገድ የጆርቶን ተወላጅ በናያ ነበር፤ በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ። በዐሥራ ሁለተኛው ወር በዐሥራ ሁለተኛው ክፍል የበላይ የዖትኒኤል ጐሣ የነጦፋ ተወላጅ የነበረው ሔልዳይ ነበር። በእርሱም ክፍል ኻያ አራት ሺህ ተረኞች ነበሩ።


ንጉሥ ዳዊት የእስራኤል ባለ ሥልጣኖች በሙሉ ወደ ኢየሩሳሌም መጥተው እንዲሰበሰቡ ትእዛዝ አስተላለፈ፤ ስለዚህ የየነገዱ መሪዎች፥ የመንግሥቱን ሥራ የሚያካሂዱ ባለሥልጣኖች የሻአለቆችና የመቶ አለቆች፥ የንጉሡንና የወንዶች ልጆቹን ንብረትና የቀንድ ከብት ተቈጣጣሪዎች እንዲሁም የቤተ መንግሥት ባለሟሎች፥ ዝነኞችና ታዋቂ የሆኑ ጀግኖች ሰዎች በሙሉ በኢየሩሳሌም ተሰበሰቡ።


ከዚህ በኋላ የጐሣ አለቆች፥ የየነገዱ መሪዎች፥ የሺህ አለቆችና የመቶ አለቆች የመንግሥት ባለሥልጣኖች በፈቃዳቸው ስጦታ ሰጡ።


ንጉሥ ሰሎሞን ለእስራኤላውያን ሁሉ፥ ለሺህ አለቆችና ለመቶ አለቆች፥ እንዲሁም ለመንግሥቱ ባለ ሥልጣኖች፥ ለቤተሰብ መሪዎችና ሕዝብ በሙሉ፥


ከእስራኤላውያንም ሁሉ መካከል ችሎታ ያላቸውን ሰዎች መረጠ፤ እነርሱንም የሺህ አለቆች፥ የመቶ አለቆች፥ የኀምሳ አለቆችና የዐሥር አለቆች አድርጎ በሕዝቡ ላይ ሾማቸው።


እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ “አንቺ በኤፍራታ ምድር የምትገኚ ቤተልሔም ሆይ! ከይሁዳ ትናንሽ ከተሞች አንድ ብትሆኚም እንኳ ከአንቺ አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘለዓለም የሆነ የእስራኤልን ሕዝብ የሚመራ ገዢ ይወጣልኛል።”


ስለዚህም ከእያንዳንዱ ነገድ የመረጣችኋቸውን የሥራ ልምድ ያላቸውን ዐዋቂዎች መሪዎች ተቀብዬ ሾምኩላችሁ። ከእነርሱም አንዳንዶቹ የሺህ አለቆች፥ አንዳንዶቹ የመቶ አለቆች፥ አንዳንዶቹም የኀምሳና የዐሥር አለቆች ሆነው የተሾሙ ነበሩ። ለነገዶችም ሁሉ ሌሎችንም ሹማምንት ሾምኩ።


ከብዙ ጊዜ በኋላ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን በዙሪያቸው ከሚገኙ ጠላቶቻቸው በማሳረፍ የሰላምን ኑሮ ሰጣቸው። በዚያን ጊዜ ኢያሱ በዕድሜው ሸምግሎ ነበር፤


ከእነርሱም አንዳንዶቹን የሺህ አለቆችና የኀምሳ አለቆች አድርጎ ይሾማል፤ ወንዶቹ ልጆቻችሁ የንጉሡ ሁዳድ አራሾችና መከር ሰብሳቢዎች ይሆናሉ፤ ሌሎችም የጦር መሣሪያና የሠረገላ ዕቃ ሠራተኞች ይሆናሉ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos