ምሳሌ 16:26 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ሰው በድካሙ ለራሱ ይደክማል፥ ከራሱም ጥፋትን ያርቃል። ጠማማ ግን በአፉ ጥፋትን ይለብሳል። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሠራተኛን የዕለት ጕርስ ፍላጎቱ ታታሪ ያደርገዋል፤ ራቡም ይገፋፋዋል። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ሠራተኛን የዕለት ጉርስ ፍላጎቱ ታታሪ ያደርገዋል፥ ረሀቡ ይጐተጉተዋልና። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሰውን ጠንክሮ እንዲሠራ የሚያደርገው የምግብ ፍላጎቱ ነው፤ ራብ ደግሞ ለሥራ ይገፋፋዋል። |
ልጄ ሆይ፥ ለራስህ ጠቢብ ብትሆን ለባልንጀራህም ጠቢብ ትሆናለህ፥ ክፉም ብትሆን ክፋትን ለብቻህ ትሸከማለህ። ሐሰትን የሚያዘጋጅ ሰው ነፋሳትን እንደሚያዘጋጅ ሰው ይመስላል። እርሱም የሚበርር ዎፍን እንደሚከተል ነው። የወይኑ ቦታ መንገዱን ተወ፤ የሚሰማራባትን መንገድ ዘነጋ፤ ወደ ምድረ በዳ ይሄዳል፥ ለጥም ወደ ተሠራች ምድርም ይሄዳል፤ የማያፈራና የማይጠቅም ገንዘብንም በእጁ ይሰበስባል።