የጦር መሣሪያቸውን ይዘው ከእናንተ ጋር በእግዚአብሔር ፊት ወደ ጦርነት ባይሻገሩ ግን ልጆቻቸውን፥ ሚስቶቻቸውን፥ ከብቶቻቸውንም በፊታችሁ ወደ ከነዓን ምድር ንዱአቸው፤ በከነዓን ምድር በእናንተ መካከል ርስታቸውን ይወርሳሉ” አላቸው።
ዘኍል 32:31 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የሮቤል ልጆችና የጋድ ልጆችም መልሰው፥ “ጌታችን ለእኛ ለአገልጋዮችህ እንደ ተናገረ እንዲሁ እናደርጋለን። አዲሱ መደበኛ ትርጒም የጋድና የሮቤል ሰዎች እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ “ባሪያዎችህ እግዚአብሔር ያለውን ያደርጋሉ፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የጋድና የሮቤልም ልጆች መልሰው እንዲህ አሉት፦ “ጌታ ለእኛ ለባርያዎችህ እንደ ተናገረ እንዲሁ እናደርጋለን። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የጋድና የሮቤል ሰዎችም እንዲህ ሲሉ መልስ ሰጡ፤ “እግዚአብሔር ያዘዘንን ሁሉ እናደርጋለን፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የጋድና የሮቤልም ልጆች መልሰው፦ እግዚአብሔር ለእኛ ለባሪያዎችህ እንደ ተናገረ እንዲሁ እናደርጋለን። |
የጦር መሣሪያቸውን ይዘው ከእናንተ ጋር በእግዚአብሔር ፊት ወደ ጦርነት ባይሻገሩ ግን ልጆቻቸውን፥ ሚስቶቻቸውን፥ ከብቶቻቸውንም በፊታችሁ ወደ ከነዓን ምድር ንዱአቸው፤ በከነዓን ምድር በእናንተ መካከል ርስታቸውን ይወርሳሉ” አላቸው።
የጦር መሣሪያችንን ይዘን በእግዚአብሔር ፊት ወደ ከነዓን ምድር እንሻገራለን፤ ከዮርዳኖስም ማዶ የወረስነው ርስት ይሆንልናል” አሉት።
እነርሱም ለኢያሱ እንዲህ ብለው መለሱለት፥ “ያዘዝኸንን ነገር ሁሉ እናደርጋለን ወደምትልከንም ስፍራ እንሄዳለን።