በኀይልህ ጩኽ፤ አትቈጥብ፤ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፤ ለሕዝቤ ኀጢአታቸውን፥ ለያዕቆብ ቤትም በደላቸውን ንገር።
ዘኍል 10:5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) መለከቱንም በምልክት ስትነፉ በምሥራቅ በኩል የሰፈሩት ይጓዙ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም መለከቱ ከፍ ባለ ድምፅ ሲነፋ በስተምሥራቅ የሰፈሩት ነገዶች ጕዞ ይጀምሩ፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የማስጠንቀቂያውንም መለከት ከፍ ባለ ድምፅ ስትነፉ በምሥራቅ በኩል የሰፈሩት ይጓዛሉ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም በአንድ መለከት ረዘም ላለ ጊዜ የማስጠንቀቂያ ድምፅ ሲሰማ በስተ ምሥራቅ የሰፈሩት ነገዶች ጒዞ ይጀምሩ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) መለከትንም ከፍ ባለ ድምፅ ስትነፉ በምሥራቅ በኩል የሰፈሩት ይጓዙ። |
በኀይልህ ጩኽ፤ አትቈጥብ፤ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፤ ለሕዝቤ ኀጢአታቸውን፥ ለያዕቆብ ቤትም በደላቸውን ንገር።
በጽዮን መለከትን ንፉ፤ በቅዱሱም ተራራዬ ላይ ዐዋጅ ንገሩ፤ በምድርም የሚኖሩ ሁሉ ይደንግጡ፤ የእግዚአብሔር ቀን መጥቶአልና፥ እርሱም ቀርቦአልና።
በመጀመሪያም የይሁዳ ልጆች ሰፈር በሥርዐታቸው ከየሠራዊቶቻቸው ጋር ተጓዘ፤ በሠራዊቱም ላይ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን አለቃ ነበረ።