ኢዮብ 38:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) አንተ ጭቃውን ከመሬት ወስደህ ሕያው ፍጥረትን ፈጥረሃልን? በምድርስ ላይ እንዲናገር አድርገሃልን? አዲሱ መደበኛ ትርጒም ምድር ከማኅተም በታች እንዳለ የሸክላ ጭቃ ቅርጿ ይወጣል፤ ቅርጿ እንደ ልብስ ቅርጽ ጐልቶ ይታያል። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ጭቃ ከማኅተም በታች እንደሚለወጥ እንዲሁም እርሱ ይለወጣል፥ ፍጥረትም ሁሉ እንደ ልብስ ተቀልሞአል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የንጋት ብርሃን ኰረብቶችንና ሸለቆዎችን እንደ ተጣጠፈ ልብስ ቈመው እንዲታዩ ያደርጋቸዋል፤ በሸክላ ላይ እንዳለ መኅተምም አጒልቶ ያሳየዋል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ጭቃ ከማኅተም በታች እንደሚለወጥ እንዲሁ እርስዋ ትለወጣለች፥ ነገርም ሁሉ እንደ ልብስ ተቀልሞአል። |