La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢሳይያስ 36:13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ራፋ​ስ​ቂ​ስም ቆሞ በታ​ላቅ ድምፅ በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ እን​ዲህ ብሎ ጮኸ፥ “የታ​ላ​ቁን የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ቃል ስሙ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

የጦር አዛዡም ቆሞ በዕብራይስጥ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንዲህ አለ፤ “የታላቁን ንጉሥ፣ የአሦርን ንጉሥ ቃል ስሙ!

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ራፋስቂስም ቆሞ በታላቅ ድምፅ በአይሁድ ቋንቋ እንዲህ ብሎ ጮኸ፦ “የታላቁን የአሦርን ንጉሥ ቃል ስሙ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ስለዚህ የአሦር ባለ ሥልጣን ከተቀመጠበት ተነሥቶ ቆመ፤ ድምፁንም ከፍ አድርጎ በዕብራይስጥ ቋንቋ እንዲህ እያለ መናገር ጀመረ፦ “የታላቁን የአሦር ንጉሥ ቃል ስሙ!

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ራፋስቂስም ቆሞ በታላቅ ድምፅ በአይሁድ ቋንቋ እንዲህ ብሎ ጮኸ፦ የታላቁን የአሦርን ንጉሥ ቃል ስሙ።

Ver Capítulo



ኢሳይያስ 36:13
14 Referencias Cruzadas  

ቅጥ​ሩን እን​ዲ​ያ​ፈ​ርሱ ከተ​ማ​ዪ​ቱ​ንም እን​ዲ​ወ​ስዱ፥ በቅ​ጥር ላይ የተ​ቀ​መ​ጡ​ትን የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን ሕዝብ ያስ​ፈ​ራ​ቸ​ውና ያስ​ደ​ነ​ግ​ጣ​ቸው ዘንድ በታ​ላቅ ድምፅ በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ቋንቋ ይጮ​ኽ​ባ​ቸው ነበር።


ኤል​ያ​ቄ​ምና ሳም​ናስ፥ ዮአ​ስም ራፋ​ስ​ቂ​ስን፥ “እኛ እን​ሰ​ማ​ለ​ንና እባ​ክህ፥ በሶ​ርያ ቋንቋ ለባ​ሪ​ያ​ዎ​ችህ ተና​ገር፤ በቅ​ጥ​ርም ላይ ባለው ሕዝብ ጆሮ በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ አት​ና​ገ​ረን” አሉት።


ራፋ​ስ​ቂስ ግን፥ “ጌታዬ ይህን ቃል እና​ገር ዘንድ ወደ እና​ን​ተና ወደ ጌታ​ችሁ ልኮ​ኛ​ልን? ከእ​ና​ንተ ጋር ኵሳ​ቸ​ውን ይበሉ ዘንድ፥ ሽን​ታ​ቸ​ው​ንም ይጠጡ ዘንድ በቅ​ጥር ላይ ለተ​ቀ​መ​ጡት ሰዎች እነ​ግ​ራ​ቸው ዘንድ አይ​ደ​ለ​ምን?” አላ​ቸው።


ራፋ​ስ​ቂ​ስም አላ​ቸው፥ “ለሕ​ዝ​ቅ​ያስ እን​ዲህ ብላ​ችሁ ንገ​ሩት፦ ታላቁ የአ​ሦር ንጉሥ እን​ዲህ ይላል፦ በማን ትተ​ማ​መ​ና​ለህ?


ምና​ል​ባት በሕ​ያው አም​ላክ ላይ ይገ​ዳ​ደር ዘንድ ጌታው የአ​ሦር ንጉሥ የላ​ከ​ውን የራ​ፋ​ስ​ቂ​ስን ቃል አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይሰማ እንደ ሆነ፥ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስለ ሰማው ቃል ይገ​ሥ​ጸው እንደ ሆነ፥ ስለ​ዚህ ለቀ​ረው ቅሬታ ጸልይ” አሉት።


ስለ​ዚህ፥ እነሆ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብር​ቱና ብዙ የሆ​ነ​ውን የወ​ንዝ ውኃ፥ የአ​ሦ​ርን ንጉ​ሥና ክብ​ሩን ሁሉ ያመ​ጣ​ባ​ቸ​ዋል፤ ወን​ዙም ሞልቶ ይወ​ጣል፤ በዳ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ሁሉ ላይ ይፈ​ስ​ሳል፤