በድንኳኑ በሁለተኛ ወገን ላሉት ሳንቆች አምስት መወርወሪያዎችን፥ በድንኳኑም በስተኋላ በምዕራብ በኩል ላሉት ሳንቆች አምስት መወርወሪያዎችን አድርግ።
ዘፀአት 26:28 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) መካከለኛውም መወርወሪያ በሳንቆቹ መካከል ከዳር እስከ ዳር ይለፍ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም መካከለኛው አግዳሚ በወጋግራዎቹ መካከል ከጫፍ እስከ ጫፍ ይተላለፍ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) መካከለኛውም መወርወሪያ በሳንቃዎች መካከል ከዳር እስከ ዳር ይለፍ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም መካከለኛውም መወርወሪያ በተራዳዎች መካከል ከዳር እስከ ዳር ይለፍ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) መካከለኛውም መወርወሪያ በሳንቆች መካከል ከዳር እስከ ዳር ይለፍ። |
በድንኳኑ በሁለተኛ ወገን ላሉት ሳንቆች አምስት መወርወሪያዎችን፥ በድንኳኑም በስተኋላ በምዕራብ በኩል ላሉት ሳንቆች አምስት መወርወሪያዎችን አድርግ።
ሳንቆቹን በወርቅ ለብጣቸው፤ ቀለበቶቻቸውንም የመወርወሪያ ቤት እንዲሆኑላቸው ከወርቅ ሥራቸው፤ መወርወሪያዎችንም በወርቅ ለብጣቸው።