ንጉሡም ደግሞ ሳሚን፥ “አንተ በአባቴ በዳዊት ላይ የሠራኸውን፥ ልብህም ያሰበውን ክፋት ሁሉ ታውቃለህ፤ እግዚአብሔርም ክፋትህን በራስህ ላይ ይመልሳል።
መክብብ 7:22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ብዙ ጊዜ ያበሳጭሃልና፤ በብዙ መንገድም ልብህን ያስከፋታልና፥ አንተ ደግሞ ሌሎችን እንደ ረገምህ ታውቃለህና። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ብዙ ጊዜ አንተ ራስህ፣ ሌሎችን እንደ ረገምህ ልብህ ያውቃልና። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) አንተ ደግሞ ሌሎችን የረገምክበትን ጊዜ ልብህ ያውቃልና። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም አንተም ራስህ ብትሆን ሁልጊዜ ሌሎችን ስትነቅፍ መኖርህን አትዘንጋ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) አንተ ደግሞ ሌሎችን እንደ ረገምህ ልብህ ያውቃልና። |
ንጉሡም ደግሞ ሳሚን፥ “አንተ በአባቴ በዳዊት ላይ የሠራኸውን፥ ልብህም ያሰበውን ክፋት ሁሉ ታውቃለህ፤ እግዚአብሔርም ክፋትህን በራስህ ላይ ይመልሳል።