ዘዳግም 24:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ያም ሰው ድሃ ቢሆን መያዣውን በአንተ ዘንድ አታሳድር። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሰውየው ድኻ ከሆነ፣ መያዣውን ከአንተ ዘንድ አታሳድርበት። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ሰውየው ድኻ ከሆነ፥ መያዣውን ከአንተ ዘንድ አታሳድርበት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ድኻ ከሆነ ደግሞ ልብሱን በመያዣነት ይዘህ አትደር። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ያም ሰው ድሃ ቢሆን መያዣውን በአንተ ዘንድ አታሳድር። |
ለብሶት እንዲተኛ እንዲባርክህም ፀሐይ ሳይገባ መያዣውን ፈጽመህ መልስለት፤ በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት ምጽዋት ይሆንልሃል።
“የመጻተኛውንና የድሃ-አደጉን፥ የመበለቲቱንም ፍርድ አታጣምምባቸው፤ የመበለቲቱንም ልብስ ለመያዣ አትውሰድባት።