ዘዳግም 20:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የሰላም ቃልም ባይመልሱልህ ከአንተም ጋር መዋጋት ቢወድዱ፥ አንተ ከተማዪቱን ትከብባለህ፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም ዕርቀ ሰላምን ባለመቀበል ውጊያን ከመረጡ፣ ከተማዪቱን ክበባት። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ዕርቀ ሰላምን ባለ መቀበል ውጊያን ከመረጡ፤ ከተማዪቱን ክበባት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ነገር ግን የዚያች ከተማ ሕዝብ አንገብርም ብለው ከአንተ ጋር መዋጋትን ቢመርጡ፥ ከተማይቱን ክበብ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የዕርቅ ቃልም ባይመልሱልህ ከአንተም ጋር መዋጋት ቢወድዱ፥ አንተ ከተማይቱን ትከብባለህ ታስጨንቃትማለህ፤ |
አምላክህ እግዚአብሔር በእጅህ አሳልፎ በሰጣት ጊዜ፥ በእርስዋ ያሉትን ወንዶች ሁሉ በሰይፍ ስለት ትገድላቸዋለህ፤