La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ነገሥት 7:8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እነ​ዚ​ያም ለም​ጻ​ሞች ወደ ሰፈሩ መጀ​መ​ሪያ ዳርቻ በመጡ ጊዜ ወደ አንድ ድን​ኳን ገብ​ተው በሉ፤ ጠጡም፤ ከዚ​ያም ወር​ቅና ብር ልብ​ስም ወሰዱ፤ ሄደ​ውም ሸሸ​ጉት፤ ተመ​ል​ሰ​ውም ወደ ሌላ ድን​ኳን ገቡ፤ ከዚ​ያም ደግሞ ወስ​ደው ሸሸጉ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ለምጽ ያለባቸውም ሰዎች ወደ ሰፈሩ አጠገብ ከደረሱ በኋላ፣ ከድንኳኖቹ ወደ አንዱ ገብተው በሉ፤ ጠጡም፤ ከዚያም ብር፣ ወርቅና ልብስ ይዘው በመሄድ ደበቁት። ተመልሰው በመምጣትም ወደ ሌላው ድንኳን ገብተው ሌሎች ነገሮችን በመውሰድ እንደዚሁ ደበቁ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

አራቱ ሰዎች ወደ ሶርያውያን ሰፈር ዳርቻ በደረሱ ጊዜ ወደ አንድ ድንኳን ውስጥ ገቡ፤ በዚያም ያገኙትን ነገር ሁሉ በልተውና ጠጥተው ያገኙትን ብር፥ ወርቅና ልብስ ይዘው ሄደው ደበቁ፤ እንደገናም ተመልሰው ወደ ሌላ ድንኳን በመግባት እንደዚያው አደረጉ፤

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

አራቱ ሰዎች ወደ ሶርያውያን ሰፈር ዳርቻ በደረሱ ጊዜ ወደ አንድ ድንኳን ውስጥ ገቡ፤ በዚያም ያገኙትን ነገር ሁሉ በልተውና ጠጥተው ያገኙትን ብር፥ ወርቅና ልብስ ይዘው ሄደው ደበቁ፤ እንደገናም ተመልሰው ወደ ሌላ ድንኳን በመግባት እንደዚያው አደረጉ፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እነዚህም ለምጻሞች ወደ ሰፈሩ መጀመሪያ ዳርቻ በመጡ ጊዜ ወደ አንድ ድንኳን ገብተው በሉ፤ ጠጡም፤ ከዚያም ወርቅና ብር ልብስም ወሰዱ፤ ሄደውም ሸሸጉት፤ ተመልሰውም ወደ ሌላ ድንኳን ገቡ፤ ከዚያም ደግሞ ወስደው ሸሸጉ።

Ver Capítulo



2 ነገሥት 7:8
7 Referencias Cruzadas  

ወደ ስውር ቦታም በደ​ረሱ ጊዜ ከእ​ጃ​ቸው ወስዶ በቤቱ ውስጥ አኖ​ራ​ቸው፤ ሰዎ​ቹ​ንም አሰ​ና​በተ።


ከዚ​ያም ወዲያ እርስ በር​ሳ​ቸው፥ “መል​ካም አላ​ደ​ረ​ግ​ንም፤ ዛሬ የመ​ል​ካም ምሥ​ራች ቀን ነው፤ እኛ ዝም ብለ​ናል፤ እስ​ኪ​ነ​ጋም ድረስ ብን​ቆይ በደ​ለ​ኞች እን​ሆ​ና​ለን፤ ኑ፥ እን​ሂድ፤ ለን​ጉሥ ቤተ​ሰ​ብም እን​ና​ገር” ተባ​ባሉ።


ገመ​ዶ​ችሽ ተበ​ጥ​ሰ​ዋል፤ ጥን​ካሬ የላ​ቸ​ው​ምና፤ ደቀ​ልሽ ዘመመ፤ ሸራ​ው​ንም መዘ​ር​ጋት አል​ቻ​ለም፤ እስ​ከ​ሚ​ያ​ዝም ድረስ አላ​ማ​ውን አል​ተ​ሸ​ከ​መም። በዚ​ያን ጊዜ የብዙ ምርኮ ተከ​ፈለ፤ ብዙ አን​ካ​ሶች እንኳ ምር​ኮ​ውን ማረኩ።


በዚ​ያም የተ​ገኙ ዐሥር ሰዎች ቀር​በው እስ​ማ​ኤ​ልን እን​ዲህ አሉት፥ “በሜ​ዳው ድልብ አለ​ንና፥ ገብ​ስና ስንዴ፥ ዘይ​ትና ማርም አለ​ንና አት​ግ​ደ​ለን፤” እር​ሱም በወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው መካ​ከል እነ​ር​ሱን መግ​ደል ተወ።


“ደግሞ መንግሥተ ሰማያት በእርሻ ውስጥ የተሰወረውን መዝገብ ትመስላለች፤ ሰውም አግኝቶ ሰወረው፤ ከደስታውም የተነሣ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ።


አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።


በዘ​ረፋ መካ​ከል አንድ ያማረ ካባ፥ ሁለት መቶ ሰቅል ብር፥ ሚዛ​ኑም አምሳ ሰቅል የሆነ ወርቅ አይቼ ተመ​ኘ​ኋ​ቸው፤ ወሰ​ድ​ኋ​ቸ​ውም፤ እነ​ሆም በድ​ን​ኳኔ ውስጥ በመ​ሬት ተሸ​ሽ​ገ​ዋል፤ ብሩም ከሁሉ በታች ነው” አለው።