La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ነገሥት 6:1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የነ​ቢ​ያ​ትም ልጆች ኤል​ሳ​ዕን፥ “እነሆ፥ በፊ​ትህ የም​ና​ድ​ር​በት ቤት ጠብ​ቦ​ናል።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

የነቢያት ማኅበር ኤልሳዕን እንዲህ አሉት፤ “እነሆ፤ በፊትህ የምንቀመጥበት ስፍራ ጠብቦናል፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

በኤልሳዕ ኀላፊነት ሥር የነበሩት የነቢያት ጉባኤ አባላት፥ “የምንኖርበት ስፍራ ጠባብ ነው፤

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

በኤልሳዕ ኀላፊነት ሥር የነበሩት የነቢያት ጉባኤ አባላት፥ “የምንኖርበት ስፍራ ጠባብ ነው፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የነቢያት ልጆች ኤልሳዕን “እነሆ፥ በፊትህ የምንቀመጥበት ስፍራ ጠብቦናል።

Ver Capítulo



2 ነገሥት 6:1
15 Referencias Cruzadas  

በኢ​ያ​ሪ​ኮም የነ​በ​ሩት የነ​ቢ​ያት ልጆች ኤል​ሳዕ ወደ እነ​ርሱ ሲመጣ ባዩት ጊዜ፥ “የኤ​ል​ያስ መን​ፈስ በኤ​ል​ሳዕ ላይ ዐር​ፎ​አል” አሉ። ሊገ​ና​ኙ​ትም መጥ​ተው በፊቱ በም​ድር ላይ ሰገ​ዱ​ለት።


በቤ​ቴ​ልም የነ​በሩ የነ​ቢ​ያት ልጆች ወደ ኤል​ሳዕ መጥ​ተው፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጌታ​ህን ከአ​ንተ ለይቶ ዛሬ እን​ደ​ሚ​ወ​ስ​ደው ዐው​ቀ​ሃ​ልን?” አሉት። እር​ሱም፥ “አዎን፥ ዐው​ቄ​አ​ለሁ፤ ዝም በሉ” አላ​ቸው።


ወደ ኢያ​ሪ​ኮም ደረሱ፤ በኢ​ያ​ሪ​ኮም የነ​በሩ የነ​ቢ​ያት ልጆች ወደ ኤል​ሳዕ ቀር​በው፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጌታ​ህን ከራ​ስህ ላይ ዛሬ እን​ዲ​ወ​ስ​ደው ዐው​ቀ​ሃ​ልን?” አሉት። እር​ሱም፥ “አዎን፥ ዐው​ቄ​አ​ለሁ፤ ዝም በሉ” አላ​ቸው።


ከነ​ቢ​ያ​ትም ልጆች አምሳ ሰዎች ሄዱ፤ በፊ​ታ​ቸ​ውም ርቀው ቆሙ፤ እነ​ዚ​ህም ሁለቱ በዮ​ር​ዳ​ኖስ ዳር ቆመው ነበር።


ከነ​ቢ​ያ​ትም ልጆች የአ​ንዱ ሚስት የሆ​ነች አን​ዲት ሴት፥ “ባሌ ባሪ​ያህ ሞቶ​አል፤ ባሪ​ያ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው እንደ ነበረ አንተ ታው​ቃ​ለህ፤ ባለ ዕዳም ሁለቱ ልጆ​ቼን ባሪ​ያ​ዎች አድ​ርጎ ሊወ​ስ​ዳ​ቸው መጥ​ቶ​አል” ብላ ወደ ኤል​ሳዕ ጮኸች።


ኤል​ሳ​ዕም ዳግ​መኛ ወደ ጌል​ጌላ ተመ​ለሰ፤ በም​ድ​ርም ላይ ራብ ነበረ፤ የነ​ቢ​ያ​ትም ልጆች በፊቱ ተቀ​ም​ጠው ነበር፤ ኤል​ሳ​ዕም ሎሌ​ውን፥ “ታላ​ቁን ምን​ቸት ጣድ፤ ለነ​ቢ​ያ​ትም ልጆች ቅጠላ ቅጠል አብ​ስ​ል​ላ​ቸው” አለው።


ወደ ዮር​ዳ​ኖ​ስም እን​ሂድ፤ ከእ​ኛም እያ​ን​ዳ​ንዱ ከዚያ ምሰሶ ያምጣ፥ የም​ና​ድ​ር​በ​ትም ቤት እን​ሥራ፥” አሉት፤ እር​ሱም፥ “ሂዱ” አለ።


አን​ተን ግን ከጠ​ላ​ትህ አፍ አድ​ኖ​ሃል፥ በበ​ታ​ች​ህም ጥልቅ ባሕር፥ ፈሳሽ ምን​ጭም አለ፥ ማዕ​ድ​ህም በስብ ተሞ​ልታ ትወ​ር​ዳ​ለች።


የእ​ሳት ኀይ​ልን አጠፉ፤ ከሰ​ይፍ ስለት አመ​ለጡ፤ ከድ​ካ​ማ​ቸው በረቱ፤ በጦ​ር​ነት ኀይ​ለ​ኞች ሆኑ፤ የባ​ዕድ ጭፍ​ሮ​ች​ንም አባ​ረሩ።


የዮ​ሴ​ፍም ልጆች ኢያ​ሱን፥ “እኛ ብዙ ሕዝብ ስን​ሆን እስከ አሁ​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ ባረ​ከን ለምን አንድ ክፍል፥ አን​ድም ዕጣ ብቻ ርስት አድ​ር​ገህ ሰጠ​ኸን?” ብለው ወቀ​ሱት።


የዳን ልጆች ነገድ ርስት በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው እነ​ዚህ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው ናቸው። የዳን ልጆ​ችም በተ​ራ​ራው ላይ የሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቋ​ቸው አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያ​ንን አላ​ስ​ጨ​ነ​ቁ​አ​ቸ​ውም። አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያ​ንም ወደ ሸለ​ቆ​ዎች ይወ​ርዱ ዘንድ አል​ፈ​ቀ​ዱ​ላ​ቸ​ውም። ከእ​ነ​ር​ሱም ከር​ስ​ታ​ቸው ዳርቻ አንድ ክፍ​ልን ወሰዱ።


ሳኦ​ልም ዳዊ​ትን ያመ​ጡት ዘንድ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላከ፤ የነ​ቢ​ያ​ት​ንም ጉባኤ አገኙ፤ ሳሙ​ኤ​ልም አለ​ቃ​ቸው ሆኖ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ቆሞ ነበረ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መን​ፈስ በሳ​ኦል መል​እ​ክ​ተ​ኞች ላይ ወረደ፤ እነ​ር​ሱም ትን​ቢት ይና​ገሩ ጀመር።