La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




1 ነገሥት 10:24 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የም​ድ​ርም ነገ​ሥት ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በልቡ ያኖ​ረ​ለ​ትን ጥበ​ቡን ይሰሙ ዘንድ የሰ​ሎ​ሞ​ንን ፊት ለማ​የት ይሹ ነበር።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ዓለሙ ሁሉ እግዚአብሔር በልቡ ያኖረውን ጥበብ ለመስማት ከሰሎሞን ጋራ መገናኘት ይፈልግ ነበር።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችም ሁሉ እግዚአብሔር የሰጠውን ጥበብ የሞላበትን ንግግር ይሰሙ ዘንድ ወደ እርሱ መምጣት ይፈልጉ ነበር።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችም ሁሉ እግዚአብሔር የሰጠውን ጥበብ የሞላበትን ንግግር ይሰሙ ዘንድ ወደ እርሱ መምጣት ይፈልጉ ነበር፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ምድርም ሁሉ እግዚአብሔር በልቡ ያኖረለትን ጥበቡን ይሰማ ዘንድ የሰሎሞንን ፊት ይመኝ ነበር።

Ver Capítulo



1 ነገሥት 10:24
13 Referencias Cruzadas  

የሳ​ባም ንግ​ሥት የሰ​ሎ​ሞ​ንን ስም፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ስም በሰ​ማች ጊዜ ሰሎ​ሞ​ንን በእ​ን​ቆ​ቅ​ልሽ ትፈ​ት​ነው ዘንድ መጣች።


እነሆ፥ እኔ እንደ ቃልህ አድ​ር​ጌ​ል​ሃ​ለሁ፤ እነ​ሆም፥ ማንም የሚ​መ​ስ​ልህ ከአ​ንተ በፊት እን​ደ​ሌለ፥ ከአ​ን​ተም በኋላ እን​ዳ​ይ​ነሣ አድ​ርጌ ጥበ​በ​ኛና አስ​ተ​ዋይ ልቡና ሰጥ​ቼ​ሃ​ለሁ።


ንጉ​ሡም የፈ​ረ​ደ​ውን ፍርድ እስ​ራ​ኤል ሁሉ ሰሙ፤ ፍር​ድን ለማ​ድ​ረግ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበብ በእ​ርሱ ላይ እንደ ነበረ አይ​ተ​ዋ​ልና ከን​ጉሡ ፊት የተ​ነሣ ፈሩ።


ስለ​ዚ​ህም ሰምቶ በሕ​ዝ​ብህ ላይ መፍ​ረድ ይችል ዘንድ፥ መል​ካ​ሙ​ንና ክፉ​ው​ንም ይለይ ዘንድ ለባ​ሪ​ያህ አስ​ተ​ዋይ ልቡና ስጠው፤ አለ​ዚ​ያማ በዚህ በታ​ላቅ ሕዝብ ላይ ይፈ​ርድ ዘንድ ማን ይች​ላል?”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰሎ​ሞ​ንን አለው፥ “ይህ በል​ብህ ነበ​ረና፥ ባለ​ጠ​ግ​ነ​ትን፥ ሀብ​ትን፥ ክብ​ርን፥ የጠ​ላ​ቶ​ች​ህ​ንም ነፍስ፥ ረጅ​ምም ዕድ​ሜን አል​ለ​መ​ን​ህም፤ ነገር ግን ባነ​ገ​ሥ​ሁህ በሕ​ዝቤ ላይ ትፈ​ርድ ዘንድ ጥብ​ብ​ንና ማስ​ተ​ዋ​ልን ለራ​ስህ ለም​ነ​ሃል።


ጥበ​ብ​ንና ማስ​ተ​ዋ​ልን እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ። ካንተ በፊት ለነ​በሩ ነገ​ሥ​ታት ያል​ተ​ሰ​ጠ​ውን፥ ከአ​ን​ተም በኋላ ለሚ​ነሡ የማ​ይ​ሰ​ጠ​ውን ብል​ፅ​ግ​ናን፥ ገን​ዘ​ብ​ንና ክብ​ርን እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ።”


እግዚአብሔር ጥበብን ይሰጣልና፤ ከፊቱም ዕውቀትና ማስተዋል ይወጣሉ፤


ባንቺ ላይ ከአ​ኖ​ር​ኋት ከክ​ብሬ የተ​ነሣ ውበ​ትሽ ፍጹም ነበ​ረና ስምሽ በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ተሰማ፥ ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፤ ለእርሱም ይሰጠዋል።