1 ዜና መዋዕል 4:39 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ለመንጎቻቸው መሰማርያ ይሹ ዘንድ ወደ ጌራራ እስኪደርሱ ድረስ ወደ ጋይ ምሥራቅ ሄዱ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም እነርሱም ለከብቶቻቸው ግጦሽ ፍለጋ ከሸለቆው በስተምሥራቅ እስካለው እስከ ጌዶር መግቢያ ድረስ ዘልቀው ሄዱ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ለመንጎቻቸው መሰማሪያ ለመፈለግ ወደ ጌዶር መግቢያ እስከ ሸለቆው ምሥራቅ ድረስ ሄዱ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም እስከ ገራር ድረስ ተሠራጩ፤ በሸለቆው በስተ ምሥራቅ በኩል ከተማይቱ በምትገኝበት ስፍራም በጎቻቸውን ያሰማሩ ነበር፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ለመንጎቻቸው መሰማርያ ይሹ ዘንድ ወደ ጌዶር መግቢያ እስከ ሸለቆው ምሥራቅ ድረስ ሄዱ። |
ሚስቱ አይሂዳም የጌዶርን አባት ያሬድን፥ የሦኮንም አባት ሔቤርን፥ የዛኖዋንም አባት ይቁቲኤልን ወለደች። እነዚህ ሞሬድ ያገባት የፈርዖን ልጅ የቢትያ ልጆች ናቸው።
ብዙና እጅግ ያማረ መሰማርያም አገኙ፤ ምድሪቱም በፊታቸው ሰፊና ጸጥተኛ ሰላም ያላትም ነበረች፤ በቀድሞም ጊዜ በዚያ ተቀምጠው የነበሩ ከካም ወገን ነበሩ።