1 ዜና መዋዕል 4:22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ኢዮአቄም፥ የካዚባ ሰዎች፥ ኢዮአስ፥ በሞዓብ አድሮ ስማቸውን፥ አብዶራንና ተቂኤም ብሎ የመለሰ ሣራፍ ነበሩ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ዮቂም፣ የኮዜባ ሰዎች፣ ኢዮአስ፣ ሞዓብን የገዛ ሣራፍና ያሹቢሌሔም። ታሪካቸውም ጥንታዊነት ያለው ነው። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ዮቂም፥ የኮዜባ ሰዎች፥ ኢዮአስ፥ ሞዓብን የገዛ ሣራፍ፥ ያሹቢሌሔም ነበሩ። ይህ መዝገብ ጥንታዊ ነው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ዮቂምና በኮዜባ ከተማ ነዋሪዎች የሆኑ ሞአባውያን ሴቶችን አግብተው በቤተልሔም ሰፍረው የነበሩት ኢዮአስና ሳራፍ ናቸው፤ (ይህ የቤተሰብ መዝገብ ጥንታዊ ነው፤) መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ዮቂም፥ የኮዜባ ሰዎች፥ ኢዮአስ፥ ሞዓብን የገዛ ሣራፍ፥ ያሹቢሌሔም ነበሩ። |
እነዚህ በነጣዔምና በጋዲራ ከንጉሡ ጋር የሚቀመጡ ሸክላ ሠራተኞች ነበሩ። እነርሱም በመንግሥቱ ጸንተው በዚያ ይኖሩ ነበር።