ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
ብቻውን ታላላቅ ብርሃናትን የሠራውን፥ ፍቅሩ ለዘለዓለም ነውና፥
ታላላቅ ብርሃናትን ፈጠረ፤ ፍቅሩ ዘለዓለማዊ ነው።
አቤቱ፥ በኢየሩሳሌም ቀን፦ “እስከ መሠረቷ ድረስ አፍርሱ አፍርሱ” ያሉአትን የኤዶምን ልጆች ዐስብ።
ጨረቃን የወቅቶች መለያ አደረግሃት፤ ፀሓይም የምትጠልቅበትን ጊዜ ታውቃለች።
ወደ ሰማይ ቀና ብለህ ፀሓይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን፣ የሰማይ ሰራዊትንም ሁሉ በምትመለከትበት ጊዜ፣ ወደ እነርሱ እንዳትሳብና እንዳትሰግድላቸው፣ አምላክህ እግዚአብሔር ከሰማይ በታች ላሉ ሕዝቦች ሁሉ ድርሻ አድርጎ የሰጣቸውንም ነገሮች እንዳታመልክ ተጠንቀቅ።