ምሳሌ 22:8 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም ክፋትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፤ የቍጣውም በትር ይጠፋል። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ክፋትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ የቁጣውም በትር ይጠፋል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፤ ቊጣውም የትም አያደርሰውም። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ሐሰትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ የሥራውንም መቅሠፍት ይፈጽማል። እግዚአብሔር ደስ ብሎት የሚሰጥ ሰውን ይወድዳል፥ ከንቱ ሥራውን ግን ይጠላል። |
እናንተ ፍልስጥኤማውያን ሆይ፤ የመታችሁ በትር ስለ ተሰበረ ሁላችሁ ደስ አይበላችሁ፤ ከእባቡ ሥር እፉኝት ይወጣልና፤ ፍሬውም ተወርዋሪ መርዘኛ እባብ ይሆናል።