ኢያሱ 10:17 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም ኢያሱም ዐምስቱ ነገሥታት በመቄዳ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸውን ሰማ፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ለኢያሱም፦ “አምስቱ ነገሥታት በመቄዳ ዋሻ ተሸሽገው ተገኝተዋል” ብለው ነገሩት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም እነዚህም አምስቱ ነገሥታት በማቄዳ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸው ለኢያሱ ተነገረው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ለኢያሱም “አምስቱ ነገሥት በመቄዳ ዋሻ ተሸሽገው ተገኙ፤” ብለው ነገሩት። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ለኢያሱም፦ አምስቱ ነገሥታት በመቄዳ ዋሻ ተሸሽገው ተገኙ ብለው ነገሩት። |