ዘፍጥረት 30:10 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም የልያ አገልጋይ ዘለፋም ለያዕቆብ ወንድ ልጅ ወለደችለት፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የልያ ባርያ ዘለፋም ወንድ ልጅን ለያዕቆብ ወለደች። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የልያ አገልጋይ ዚልፋ ለያዕቆብ ወንድ ልጅ ወለደችለት። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የልያ አገልጋይ ዘለፋም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅንም ለያዕቆብ ወለደች። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የልያ ባሪያ ዘለፋም ወንድ ልጅን ለያዕቆብ ወለደች። |
ከጋድ ዝርያ፦ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።
እጅግ ብዙ የሆነ የቀንድ ከብት፣ የበግና የፍየል መንጋዎች የነበሯቸው የሮቤልና የጋድ ነገዶች የኢያዜርና የገለዓድ ምድር ለከብት ምቹ ስፍራዎች መሆናቸውን አዩ።