“ትእዛዞቼን ጠብቁ፤ አንዱን እንስሳ ከሌላው ጋር አታዳቅል፥ በአንድ እርሻ ላይ ሁለት ዐይነት እህል አትዝራ፥ ከሁለት ዐይነት ነገር ተፈትሎ የተሠራ ልብስ አትልበስ።
ዘዳግም 22:11 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም “ሱፍና በፍታ ተቀላቅሎ አብሮ የተሠራ ልብስ አትልበስ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሱፍና በፍታ አንድ ላይ ተፈትሎ የተሠራ ልብስ አትልበስ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) “ሱፍና በፍታ ተቀላቅሎ አብሮ የተሠራ ልብስ አትልበስ። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ከተልባ እግርና ከበግ ጠጕር በአንድነት የተሠራ ልብስ አትልበስ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ከተልባ እግርና ከበግ ጠጉር በአንድነት የተሠራ ልብስ አትልበስ። |
“ትእዛዞቼን ጠብቁ፤ አንዱን እንስሳ ከሌላው ጋር አታዳቅል፥ በአንድ እርሻ ላይ ሁለት ዐይነት እህል አትዝራ፥ ከሁለት ዐይነት ነገር ተፈትሎ የተሠራ ልብስ አትልበስ።
ቀጥሎም ኢየሱስ፥ እንዲህ ሲል አንድ ምሳሌ ነገራቸው፦ “የአዲስ ልብስ ዕራፊ በአሮጌ ልብስ ላይ የሚጥፍ ማንም የለም፤ ይህን ቢያደርግ ግን አዲሱን ልብስ ይቀደዋል፤ አዲሱም ዕራፊ ለአሮጌው ልብስ አይስማማም፤