መጽሐፈ ዮዲት 12:7 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ሆሎፎርኒስም እንዳይከለክሏት ዘበኞቹን አዘዛቸው። በሰፈሩ ሦስት ቀን ቆየች፤ በየሌሊቱም ወደ ቤቱሊያ ሸለቆ እየሄደች በሰፈሩ በሚገኘው የምንጭ ውኃ ትታጠብ ነበር። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ሆሎፎርኒስም እንዳይከለክሏት የሚጠብቁትን ሰዎች አዘዛቸው፤ ከዚህ በኋላም በሰፈር ሦስት ቀን አደረች፤ በየሌሊቱም እየወጣች ወደ ቤጤሌዋ ሸለቆ ትወርድ ነበር፤ ሌሊትም በሰፈሩ ምንጭ ውኃ ትታጠብ ነበር፤ ሌሊትም ወጥታ በምንጩ ውኃ ትጠመቅ ነበር። |