Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ዮዲት 12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ዮዲት በሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ እንደ ተጋ​በ​ዘች

1 የብር ዕቃ ወደ​ሚ​ቀ​መ​ጥ​በት ድን​ኳን ያገ​ቧት ዘንድ አዘዘ፤ ለእ​ር​ሱም ከሚ​ያ​ዘ​ጋ​ጁት ምግብ ይመ​ግ​ቧት ዘንድ፥ እርሱ ከሚ​ጠ​ጣው መጠ​ጥም ያጠ​ጧት ዘንድ አዘዘ።

2 ዮዲ​ትም፥ “ካመ​ጣ​ሁት እህል እመ​ገ​ባ​ለሁ እንጂ በደል እን​ዳ​ይ​ሆ​ን​ብኝ ከእ​ርሱ አል​መ​ገ​ብም” አለች።

3 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም፥ “ያመ​ጣ​ሽ​ውስ ቢያ​ል​ቅ​ብሽ እንደ እርሱ ያለ ከየት አም​ጥ​ተን እን​ሰ​ጥ​ሻ​ለን? ከወ​ገ​ኖ​ችሽ ስንኳ ካንቺ ጋር ያለ ሰው የለም” አላት።

4 ዮዲ​ትም፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእኔ ቃል የመ​ከ​ረ​ውን እስ​ኪ​ያ​ደ​ርግ ድረስ እኔ አገ​ል​ጋ​ይህ የያ​ዝ​ሁ​ትን እን​ዳ​ል​ጨ​ርስ ጌታዬ ሕያው ነፍ​ስ​ህን” አለ​ችው።

5 የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም አሽ​ከ​ሮች ወደ ድን​ኳኑ አገ​ቧት፤ እስከ እኩለ ሌሊ​ትም ድረስ ተኛች። ሌሊ​ቱም ከመ​ን​ጋቱ በፊት በእ​ኩለ ሌሊት ተነ​ሣች፤

6 “እኔ አገ​ል​ጋ​ይህ ለጸ​ሎት እን​ድ​ወጣ ይፈ​ቅ​ዱ​ልኝ ዘንድ እዘ​ዝ​ልኝ” ብላ ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ላከች።

7 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም እን​ዳ​ይ​ከ​ለ​ክ​ሏት የሚ​ጠ​ብ​ቁ​ትን ሰዎች አዘ​ዛ​ቸው፤ ከዚህ በኋ​ላም በሰ​ፈር ሦስት ቀን አደ​ረች፤ በየ​ሌ​ሊ​ቱም እየ​ወ​ጣች ወደ ቤጤ​ሌዋ ሸለቆ ትወ​ርድ ነበር፤ ሌሊ​ትም በሰ​ፈሩ ምንጭ ውኃ ትታ​ጠብ ነበር፤ ሌሊ​ትም ወጥታ በም​ንጩ ውኃ ትጠ​መቅ ነበር።

8 ከው​ኃ​ውም በወ​ጣች ጊዜ ስለ ወገ​ኖ​ችዋ ልጆች መነ​ሣት መን​ገ​ድ​ዋን ያቃ​ና​ላት ዘንድ ወደ እስ​ራ​ኤል አም​ላክ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትጸ​ልይ ነበር።

9 ከዚ​ህም በኋላ ትመ​ለስ ነበር፤ በሰ​ፈ​ርም በን​ጽ​ሕና ትቀ​መጥ ነበር፤ ማታ ማታም ትመ​ገብ ነበር።

10 ከዚ​ህም በኋላ በአ​ራ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ለአ​ሽ​ከ​ሮቹ ለብ​ቻ​ቸው ምሳ አደ​ረገ፤ ሌላ ሰው ማን​ንም ወደ ምሳው አል​ጠ​ራም።

11 የገ​ን​ዘቡ ሁሉ መጋቢ የሆ​ነ​ውን ጃን​ደ​ረባ ባግ​ዋን፥ “በአ​ንተ ዘንድ ያለች ያችን ዕብ​ራ​ዊት ሴት ወደ እኛ ትመጣ ዘንድ አባ​ብ​ል​ልኝ፤ ከእኛ ጋር ትብላ፤ ትጠ​ጣም፤ ሄደ​ህም ንገ​ራት።

12 እን​ዲህ ያለች ሴት አግ​ኝ​ተን ባና​ነ​ጋ​ግ​ራት ለእኛ ዕፍ​ረ​ታ​ችን ነውና፥ ባን​ገ​ና​ኛ​ትም ይስ​ቁ​ብ​ና​ልና” አለው።

13 ባግ​ዋም ከሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ዘንድ ወጥቶ ወደ እርሷ ገባ፥ “መልከ መል​ካም የሆ​ንሽ አንቺ ልጄ ሆይ! ወደ ጌታዬ መም​ጣ​ትን እንቢ አት​በዪ፤ በእ​ርሱ ዘንድ ትከ​ብ​ሪ​ያ​ለሽ፤ ከእ​ር​ሱም ጋራ ወይ​ንን ጠጥ​ተሽ ደስ ይል​ሻል፤ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ቤት ከሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ሉት ከአ​ሦር ልጆ​ችም እንደ አን​ዲቱ ትሆ​ኛ​ለሽ” አላት።

14 ዮዲ​ትም አለ​ችው፥ “ጌታ​ዬን እንቢ እለው ዘንድ እኔ ማን ነኝ? ወገ​ኔስ ማን ነው? የወ​ደ​ድ​ኸ​ውን ሁሉ በፊ​ትህ ፈጥኜ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ እስ​ክ​ሞ​ትም ድረስ ለእኔ ደስታ ይሆ​ን​ል​ኛል፤”

15 ተነ​ሥ​ታም ልብ​ሷን ለበ​ሰች፤ የሴ​ቶ​ች​ንም ጌጥ ሁሉ ፈጽማ አጌ​ጠች፤ ብላ​ቴ​ና​ዋም ከእ​ርሷ ጋራ ሄደች፤ ከባ​ግዋ የተ​ቀ​በ​ለ​ች​ውን፥ በማ​ደ​ሪ​ያዋ ያነ​ጠ​ፈ​ላ​ትን፥ ምሳም ስት​በላ የም​ት​ቀ​መ​ጥ​በ​ትን ምን​ጣ​ፏን በሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ፊት በም​ድር ላይ አነ​ጠ​ፈ​ች​ላት።

16 ዮዲ​ትም ወደ እርሱ ገብታ ተቀ​መ​ጠች፤ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም ልቡ​ናው በእ​ርሷ ታወከ፤ ከእ​ር​ሷም ጋር ይተኛ ዘንድ ሰው​ነቱ ፈጽማ ጐመ​ጀች፤ ከአ​ያ​ትም ጀምሮ እር​ሷን እስ​ከ​ሚ​ያ​ባ​ብ​ል​በት ጊዜ ይጠ​ብ​ቃት ነበር።

17 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም ዮዲ​ትን፥ “ጠጥ​ተሽ ከእኛ ጋር ደስ ይበ​ልሽ” አላት።

18 ዮዲ​ትም፥ “ከተ​ወ​ለ​ድሁ ጀምሮ ከዘ​መኔ ሁሉ ይልቅ ሕይ​ወቴ ዛሬ ከብ​ራ​ለ​ችና ጌታዬ እጠ​ጣ​ለሁ” አለ​ችው።

19 አገ​ል​ጋ​ይ​ዋም ያዘ​ጋ​ጀ​ች​ላ​ትን ተቀ​ብላ በፊቱ በላች፤ ጠጣ​ችም።

20 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም ስለ እርሷ ደስ አለው፤ ከተ​ወ​ለ​ደም ጀምሮ አን​ዲት ቀን ስንኳ እን​ደ​ዚያ ያል​ጠ​ጣ​ውን ብዙ ወይን አብ​ዝቶ ጠጣ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos