መሳፍንት 18:22 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ከሚካ ቤት ጥቂት ራቅ እንዳሉም፥ የሚካ ጎረቤቶች ለርዳታ ተጠርተው ተሰበሰቡ፤ የዳን ሰዎችንም ተከታትለው ደረሱባቸው። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ከሚካ ቤት ጥቂት ራቅ እንዳሉም፣ የሚካ ጎረቤቶች ለርዳታ ተጠርተው ተሰበሰቡ፤ የዳን ሰዎችንም ተከታትለው ደረሱባቸው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከቤቱ ራቅ ብለው ከሄዱ በኋላ ሚካ ጐረቤቶቹን ሰብስቦ በመከተል ከዳን የመጡትን ሰዎች ደረሰባቸውና፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ከሚካም ቤት ሳይርቁ ሚካና የሚካ ጎረቤቶች ጮኹ፤ የዳንንም ልጆች ተከትለው ደረሱባቸው። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ከሚካም ቤት በራቁ ጊዜ የሚካ ጐረቤቶች ተሰበሰቡ፥ የዳንንም ልጆች ተከትለው ደረሱባቸው። |
ከበሰተኋላቸው ሆነው ሲጮሁባቸውም፥ የዳን ሰዎች ወደ ኋላቸው ዞረው ሚካን፥ “ሰዎችህን ለውጊያ አሰባስበህ መምጣትህ ምን ሆነህ ነው?” አሉት።