ዘፀአት 18:2 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የሙሴ አማት ይትሮ መልሷት የነበረችውን የሙሴን ሚስት ጺፖራን ወሰደ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሙሴ ሚስቱን ሲፓራን ከመለሳት በኋላ ዐማቱ ዮቶር እርሷንና ሁለት ወንድ ልጆቿን ተቀብሏቸው ነበር። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ስለዚህም በእርሱ ዘንድ ትቶአት ሄዶ የነበረችውን የሙሴን ሚስት ጺጳራን፥ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በዚያ ጊዜ የሙሴ አማት ዮቶር ትቶአት የነበረውን የሙሴን ሚስት ሲፓራን፥ ሁለቱንም ልጆችዋን ወሰደ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በዚያን ጊዜ የሙሴ አማት ዮቶር መልሶአት የነበረውን የሙሴን ሚስት ሲፓራን ሁለቱንም ልጆቿን ወሰደ። |