1 ዜና መዋዕል 1:50 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በኣልሐናንም ሞተ፥ በእርሱም ፋንታ ሃዳድ ነገሠ፤ የከተማይቱም ስም ፋዑ ነበረ፤ ሚስቱም የሜዛሃብ ልጅ የመጥሬድ ልጅ መሄጣብኤል ነበረች፤ ሃዳድም ሞተ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም በኣልሐናን ሲሞት ሃዳድ በምትኩ ነገሠ። የእርሱም ከተማ ስም ፋዑ ነው፤ የሚስቱም ስም መሄጣብኤል ሲሆን እርሷም የሜዛሃብ ልጅ የማጥሬድ ልጅ ነበረች። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም በዓልሐናን በሞተ ጊዜ የፋዑ ተወላጅ የነበረው ሀዳድ ነገሠ፤ ሚስቱም መሄጣብኤል የምትባል የዛሀብ የልጅ ልጅ የማናሬድ ልጅ ነበረች። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የአክቦር ልጅ በኣልሐናንም ሞተ፤ በእርሱም ፋንታ የባራድ ልጅ አዳድ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ፌጎር ነበረ፤ ሚስቱም የሚዛሃብ ልጅ የመጥሬድ ልጅ መሄጣብኤል ነበረች። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በኣልሐናንም ሞተ፤ በእርሱም ፋንታ ሐዳድ ነገሠ፤ የከተማይቱም ስም ፋዑ ነበረ፤ ሚስቱም የሜዛሃብ ልጅ የመጥሬድ ልጅ መሄጣብኤል ነበረች፤ ሃዳድም ሞተ። |
የዓክቦር ልጅ በኣል-ሐናንም ሞተ፥ በስፍራውም ሃዳር ነገሠ፥ የከተማውም ስም ፋዑ ነው፥ ሚስቱም የሜዛሃብ ልጅ ማጥሬድ የወለደቻት መሄጣብኤል ትባል ነበር።