ዘዳግም 22:16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የብላቴናዪቱም አባት ሽማግሌዎቹን፦ እኔ ለዚህ ሰው ልጄን ዳርሁለት፤ እርሱም ጠላት፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም የልጅቱም አባት ለአለቆቹ እንዲህ ይበል፤ “ልጄን ለዚህ ሰው ዳርሁለት፤ እርሱ ግን ጠላት፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የብላቴናይቱም አባት ሽምግሌዎቹን፦ ‘እኔ ለዚህ ሰው ልጄን ዳርሁለት እርሱም ጠላት፥’ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የልጅቱም አባት እንዲህ ብሎ ያስረዳ፦ ‘እኔ ሴት ልጄን ለዚህ ሰው ድሬለት ነበር፤ እነሆ፥ አሁን እርሱ የጠላት መሆኑን ገልጦአል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የብላቴናይቱም አባት ሽምግሌዎቹን፦ እኔ ለዚህ ሰው ልጄን ዳርሁለት እርሱም ጠላት፤ |
የብላቴናዪቱ አባትና እናት የልጃቸውን የድንግልናዋን ልብስ ወስደው በበሩ አደባባይ ወደ ተቀመጡ ወደ ከተማ ሽማግሌዎች ያምጡት፤
እነሆም፦ በልጅህ ድንግልና አላገኘሁባትም ብሎ የነውር ነገር አወራባት፤ የልጄም የድንግልናዋ ልብስ ይኸው ይላቸዋል። በከተማም ሽማግሌዎች ፊት ልብሱን ይዘረጋሉ።