ታላላቅ ብርሃናትን ፈጠረ፤ ፍቅሩ ዘለዓለማዊ ነው።
ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
ብቻውን ታላላቅ ብርሃናትን የሠራውን፥ ፍቅሩ ለዘለዓለም ነውና፥
አቤቱ፥ በኢየሩሳሌም ቀን፦ “እስከ መሠረቷ ድረስ አፍርሱ አፍርሱ” ያሉአትን የኤዶምን ልጆች ዐስብ።
ጨረቃን የወቅቶች ምልክት እንድትሆን፥ ፀሐይ የሚጠልቅበትን ጊዜ እንዲያውቅ አድርገሃል።
በሰማይ ላይ የምታዩአቸውን ፀሐይንና ጨረቃን ወይም ከዋክብትን ወይም የሰማይን ሠራዊት ሁሉ በማምለክና ለእነርሱ በመስገድ እንዳትፈተኑ ተጠንቀቁ፤ እግዚአብሔር አምላካችሁ እነዚህን ሁሉ ሌሎች ሕዝቦች ብቻ ያመልኩአቸው ዘንድ አሳልፎ ሰጥቶአቸዋል።