ሰነፍ ሰው ከአጥፊ ሰው ተለይቶ አይታይም፤
ለሥራው ደንታ የሌለው ሰው፣ የአጥፊ ወንድም ነው።
በሥራው ታካች የሚሆን የሀብት አጥፊ ወንድም ነው።
በሥራው ራሱን የማያድን፥ ራሱን ለሚያጠፋ ወንድም ነው።
ከሰው ተለይቼ ለቀበሮ ወንድም ለሰጎንም ባልንጀራ ሆንኩ።
ስንፍና ያደኸያል፤ ተግቶ መሥራት ግን ያበለጽጋል፤
የሐሜተኛ ሰው ቃል እንደ ጣፋጭ ምግብ ደስ እያሰኘ እስከ ውስጥ ሰውነት ድረስ ይወርዳል።
ስንፍና እንቅልፍን ያስከትላል፤ ስለዚህም ሰነፍ ሰው ይራባል።
ከአባቱና ከእናቱ ሰርቆ “ኃጢአት አላደረግሁም” የሚል ሰው ከማንኛውም አጥፊ ሰው የተሻለ አይደለም።
ጌታው ግን እንዲህ አለው፤ ‘አንተ ክፉና ሰነፍ አገልጋይ! ካልዘራሁበት እንደማጭድ ካልበተንኩበት እንደምሰበስብ የምታውቅ ከሆነ፥
ሳትታክቱ የጋለ መንፈስን ተከትላችሁ ጌታን አገልግሉ።
የምንመኘውም በእምነትና በትዕግሥት ጸንተው ተስፋ የተሰጣቸውን ነገር የሚወርሱትን ሰዎች እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንድትሆኑ አይደለም።