ሕዝቅኤል 34:7 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ስለዚህ እረኞች ሆይ፥ የጌታን ቃል ስሙ፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም “ ‘ስለዚህ እናንተ እረኞች፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም “አሁንም እናንተ እረኞች! እኔ እግዚአብሔር የምላችሁን ስሙ፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) “ስለዚህ እረኞች ሆይ! የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ስለዚህ፥ እረኞች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፥ |
አንተም እንዲህ ትላቸዋለህ፦ “ጌታ እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በዚህች ምድር የሚኖሩትን ሁሉ፥ በዳዊት ዙፋን የሚቀመጡትን ነገሥታት ካህናቱንም ነቢያቱንም በኢየሩሳሌምም የተቀመጡትን ሁሉ በስካር እሞላቸዋለሁ።
ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔም ሕያው ነኝና እረኛ ስለ ሌለ እረኞቼም በጎቼን ስላልፈለጉ እረኞችም ራሳቸውን እንጂ በጎቼን ስላላሰማሩ፥ በጎቼ ንጥቂያ ሆነዋልና፥ በጎቼም ለምድር አራዊት ሁሉ መብል ሆነዋልና