“አንተ የደግ ሰው ልጅ ነህ” ብሎ መረቀው፤ የጦቢትም ዐይኖች እንደ ጠፉ ነገረው። የጦቢትም ዐይኖች እንደ ጠፉ በሰማ ጊዜ አዝኖ አለቀሰ።
ቀጥሎም “ተባረክ ልጄ! የደግ አባት ልጅ ነህ። እንዲህ ያለ ብሩህና መልካም የሚሠራ ሰው ዐይኖቹን ማጣቱ እንዴት ያሳዝናል” አለ። በዘመዱ ጦቢያ አንገት ላይ ተጠምጥሞ አለቀሰ።