መጽሐፈ ጦቢት 4:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) “ልጄ! ራስህን ከዝሙት ጠብቅ፤ ከአባቶችህ ዘር ሁሉ አስቀድመህ ሚስት አግባ። ከዘመዶችህ ካልሆነች ከባዕድ ወገን ግን አታግባ። እኛ ከጥንት ጀምረው ከነበሩ ከነቢያት ከኖኅና ከአብርሃም ፥ ከይስሐቅና ከያዕቆብ ልጆች ወገን ነንና፤ ልጄ ሆይ፥ ሁሉም ከአባቶቻቸው ትውልድ ሚስት እንዳገቡ አስብ፤ በልጆቻቸውም እንደ ተባረኩ፥ ዘሮቻቸውም ምድርን እንደ ወረሷት አስብ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ልጄ ሆይ ከዝሙት ተጠንቀቅ፥ ከሁሉ አስቀድመህ ከአባቶችህ ወገን የሆነች ሴት አግባ፥ እኛ የነቢያት ልጆች ነንና ከአባትህ ነገድ ያልሆነችውን ባዕድ ሴት አታግባ። ልጄ ሆይ ከጥንት ጀምሮ የነበሩትን አባቶቻችንን ኖኀን፥ አብርሃምን፥ ይስሐቅን፥ ያዕቆብን አስብ፤ ሁሉም ሚስት የወሰዱት ከወገኖቻቸው ነው፤ ስለዚህም በልጆቻቸውም የተባረኩ ሆኑ፤ ዘራቸውም ምድርን ይወርሳል። |