Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ጦቢት ለልጁ የሰ​ጠው ምክር

1 በዚ​ያ​ችም ቀን ጦቢት በሜ​ዶን ክፍል በራ​ጌስ ለገ​ባ​ኤል አደራ ስላ​ስ​ጠ​በ​ቀው ብር አሰበ።

2 አስ​ቦም እን​ዲህ አለ፥ “እነሆ ልሙት ብዬ ለመ​ንሁ፤ እን​ግ​ዲህ ልጄን ጦብ​ያን ጠርቼ ሳል​ሞት የማ​ል​ነ​ግ​ረው ለም​ን​ድን ነው?”

3 ጠር​ቶም እን​ዲህ አለው፥ “ልጄ በሞ​ትሁ ጊዜ በመ​ል​ካሙ ቅበ​ረኝ፤ እና​ት​ህ​ንም ጠብ​ቃት፤ በሕ​ይ​ወ​ት​ህም ዘመን ሁሉ አክ​ብ​ራት፤ የወ​ደ​ደ​ች​ው​ንም አድ​ር​ግ​ላት፤ አታ​ሳ​ዝ​ና​ትም።

4 ልጄ፥ በማ​ኅ​ፀን ባንተ ብዙ መከራ እንደ ተቀ​በ​ለች አስብ፤ በሞ​ተ​ችም ጊዜ በእኔ ዘንድ ባንድ መቃ​ብር ቅበ​ራት።

5 ልጄ ሆይ! በዘ​መኑ ሁሉ ፈጣ​ሪህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አስ​በው፤ በደ​ል​ንና ትእ​ዛ​ዙን መካ​ድን አት​ው​ደድ፤ በሕ​ይ​ወ​ት​ህም ዘመን ሁሉ ጽድ​ቅን ሥራ፤ በዐ​መፅ መን​ገ​ድም አት​ሂድ።

6 ጽድ​ቅን ከሠ​ራ​ሃት በመ​ን​ገ​ድህ ሁሉና በሠ​ራ​ኸው ሥራ ሁሉ ትከ​ና​ወ​ና​ለህ፤ ጽድ​ቅ​ንም ለሚ​ሠ​ሩ​ዋት ሁሉ ይከ​ና​ወ​ን​ላ​ቸ​ዋል።

7 ከገ​ን​ዘ​ብህ ምጽ​ዋት ስጥ፤ ምጽ​ዋ​ት​ንም በም​ት​መ​ጸ​ውት ጊዜ በገ​ን​ዘ​ብህ አት​ን​ፈግ፤ ከድ​ኃም ፊት​ህን አት​መ​ልስ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊቱን ከአ​ንተ አይ​መ​ል​ስም።

8 ባለህ መጠን የሚ​ቻ​ል​ህን ያህል ምጽ​ዋት አድ​ርግ።

9 ጥቂ​ትም ቢሆን ለመ​ስ​ጠት አት​ፈር፤ ምጽ​ዋት መስ​ጠት መል​ካም ድል​ብን ታደ​ል​ብ​ል​ሃ​ለ​ችና።

10 ምጽ​ዋት በመ​ከራ ቀን ከሞት ታድ​ና​ለ​ችና፤ ወደ ጨለ​ማም ከመ​ሄድ ትጠ​ብ​ቅ​ሃ​ለ​ችና።

11 ምጽ​ዋ​ትም ለሚ​ያ​ደ​ር​ጋት ሁሉ በል​ዑል ፊት መል​ካም ስጦታ ናት።

12 “ልጄ! ራስ​ህን ከዝ​ሙት ጠብቅ፤ ከአ​ባ​ቶ​ችህ ዘር ሁሉ አስ​ቀ​ድ​መህ ሚስት አግባ። ከዘ​መ​ዶ​ችህ ካል​ሆ​ነች ከባ​ዕድ ወገን ግን አታ​ግባ። እኛ ከጥ​ንት ጀም​ረው ከነ​በሩ ከነ​ቢ​ያት ከኖ​ኅና ከአ​ብ​ር​ሃም ፥ ከይ​ስ​ሐ​ቅና ከያ​ዕ​ቆብ ልጆች ወገን ነንና፤ ልጄ ሆይ፥ ሁሉም ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ትው​ልድ ሚስት እን​ዳ​ገቡ አስብ፤ በል​ጆ​ቻ​ቸ​ውም እንደ ተባ​ረኩ፥ ዘሮ​ቻ​ቸ​ውም ምድ​ርን እንደ ወረ​ሷት አስብ።

13 አሁ​ንም ልጄ ሆይ፥ ባል​ን​ጀ​ራ​ህን ውደድ፤ በባ​ል​ን​ጀ​ራህ፥ በወ​ገ​ኖ​ችህ ወን​ዶች ልጆ​ችና በወ​ገ​ኖ​ችህ ሴቶች ልጆች ልብ​ህን አታ​ስ​ታ​ብይ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ወገን ሚስት አግባ። ትዕ​ቢት ባለ​ች​በት ዘንድ ውር​ደት አለ​ችና፥ ብዙ ሁከ​ትም አለና፤ ስን​ፍ​ናም ባለ​ች​በት ዘንድ ችግር አለች፤ ታላቅ ድህ​ነ​ትም አለ፤ ስን​ፍና የረ​ኃብ እናት ናትና።

14 የተ​ገ​ዛ​ልህ ሁሉ ደመ​ወዝ ባንተ ዘንድ አይ​ደር፤ በጊ​ዜው ስጠው እንጂ። ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብት​ገዛ ዋጋህ ይበ​ዛ​ል​ሃ​ልና፤ ራስ​ህን ዕወቅ፤ በሥ​ራ​ህና በጠ​ባ​ይህ ሁሉ ጠቢብ ሁን።

15 ለራ​ስህ የም​ት​ጠ​ላ​ውን ለማ​ንም አታ​ድ​ርግ፤ ለመ​ስ​ከ​ርም ወይ​ንን አት​ጠጣ፤ ከሰ​ካ​ራ​ሞ​ችም ጋር በጎ​ዳና አት​ሂድ።

16 ከእ​ህ​ል​ህም ለተ​ራበ፥ ከል​ብ​ስ​ህም ለተ​ራ​ቈተ ስጥ፤ ከተ​ረ​ፈ​ህም ሁሉ ለም​ጽ​ዋት አድ​ርግ።

17 እህ​ል​ህ​ንም በጻ​ድ​ቃን መቃ​ብር ላይ ዝራ፤ ለኀ​ጥ​ኣን ግን አት​ስጥ።

18 በጠ​ቢ​ባን ዘንድ ምክ​ርን ፈልግ፤ የም​ት​ረ​ባ​ህ​ንም ምክር አታ​ቃል።

19 በየ​ጊ​ዜ​ውም ፈጣ​ሪህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ነው፤ ጎዳ​ና​ህም የቀና ይሆን ዘንድ ወደ እርሱ ጸልይ፤ በሥ​ራህ ሁሉና በጎ​ዳ​ናህ ሁሉ ያከ​ና​ው​ን​ል​ሃል። በጎ​ውን ሁሉ ከሚ​ሰጥ ከእ​ርሱ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቀር ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያል​ሆነ አሕ​ዛብ ሁሉ የሚ​መ​ክ​ሩት ምክር ከንቱ ነውና። የወ​ደ​ደ​ውን ያዋ​ር​ደ​ዋል፤ እር​ሱም እንደ ወደደ ይሆ​ናል። አሁ​ንም ልጄ ሆይ ትእ​ዛ​ዜን አስብ፤ ከል​ብ​ህም አይ​ጥፋ።


ጦቢት ለገ​ባ​ኤል አደራ ስለ ሰጠው ገን​ዘብ

20 “አሁ​ንም በሜ​ዶን ክፍል በራ​ጊስ ሰው በግ​ብ​ር​ያል ልጅ በገ​ባ​ኤል ዘንድ አደራ ስላ​ስ​ጠ​በ​ቅ​ሁት ስለ ዐሥሩ የብር መክ​ሊት እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ።

21 ልጄ ሆይ! ከድ​ህ​ነት የተ​ነሣ አት​ፍራ። ድሆች ባንተ ዘንድ ብዙ በረ​ከ​ትን ይቀ​በ​ላ​ሉና፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ብት​ፈ​ራው ከኀ​ጢ​አ​ትም ሁሉ ብት​ርቅ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኘ​ውን ሥራ በፊቱ ብታ​ደ​ርግ ብዙ በረ​ከት ባንተ ዘንድ ይኖ​ራል።”

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች