መጽሐፈ ጦቢት 5:13 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) እርሱም “ስሜ አዛርያ ነው፥ ከዘመዶችህ አንዱ የሆነው የታላቁ አናንያ ልጅ ነኝ” አለው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ጦቢትም አለው፥ “አንተ ወንድሜ ደኅና ነህን? ወገንህንና ሀገርህን ዐውቅ ዘንድ መርምሬአለሁና አትንቀፈኝ፤ ነገር ግን አንተ በእውነቱ ከደግና ከተባረከ ወገን ነህ፤ እኔም የታላቁ የሴምዩን ልጆች አናንያንና ኢታያንን ዐውቃቸዋለሁ፤ እንሰግድ ዘንድ ከእነርሱ ጋር አብረን ወደ ኢየሩሳሌም ሄደን ነበር፤ በኵራቱንና የእህላችንን ዐሥራት ወስደን ነበር፤ ነገር ግን በአባቶቻችን በደል አልበደልንም። |