Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


መል​አኩ ሩፋ​ኤል ከጦ​ብያ ጋር እንደ ሄደ

1 ጦብ​ያም መለሰ እን​ዲ​ህም አለ፥ “አባቴ! ያዘ​ዝ​ኸ​ኝን ሁሉ አደ​ር​ጋ​ለሁ።

2 ነገር ግን ከማ​ላ​ው​ቀው ሰው ያን ብር መቀ​በል እን​ዴት እች​ላ​ለሁ?”

3 እር​ሱም ደብ​ዳቤ ሰጠው፤ እን​ዲ​ህም አለው፥ “ከአ​ንተ ጋር የሚ​ሄድ ሰው ፈልግ፤ እኔም በሕ​ይ​ወት ሳለሁ ደመ​ወ​ዙን እሰ​ጠ​ዋ​ለሁ፤ ሄደ​ህም ያንን ብር ተቀ​በል።”

4 እር​ሱም ሰውን ሊፈ​ልግ ሄዶ መል​አ​ኩን ሩፋ​ኤ​ልን አገ​ኘው፤ ነገር ግን መል​አክ እንደ ሆነ አላ​ወ​ቀም።

5 እር​ሱም አለው፥ “ሀገ​ሩን ታውቅ እንደ ሆነ ወደ ሜዶን ክፍል ወደ ራጊስ ከኔ ጋራ መሄድ ትች​ላ​ለ​ህን?”

6 መል​አ​ኩም እን​ዲህ አለው፥ “ከአ​ንተ ጋር እሄ​ዳ​ለሁ፤ መን​ገ​ዱ​ንም ዐው​ቃ​ለሁ፤ በገ​ባ​ኤ​ልም ዘንድ ነበ​ርሁ።”

7 ጦብ​ያም፥ “ላባቴ እስ​ክ​ነ​ግ​ረው ድረስ ቈየኝ” አለው።

8 እር​ሱም፥ “ሂድ፤ አት​ቈይ” አለው፤ ለአ​ባ​ቱም፥ “ከእኔ ጋር የሚ​ሄድ እነሆ አገ​ኘሁ” አለው። እር​ሱም፥ “ከማን ወገን እንደ ሆነ፥ ካን​ተም ጋራ ለመ​ሄድ የታ​መነ እንደ ሆነ ዐውቅ ዘንድ ወደ እኔ ጥራው” አለው።

9 ጠራ​ውና ገባ፤ እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም እጅ ተነ​ሣሡ።

10 ጦቢ​ትም፥ “አንተ ወን​ድሜ! ከማን ወገን ነህ? ከወ​ዴ​ትስ ሀገር ነህ?” አለው።

11 መል​አ​ኩም፥ “ወገ​ኔ​ንና ሀገ​ሬን ትመ​ረ​ምር? ወይስ ከል​ጅህ ጋራ የም​ሄ​ድ​በ​ትን ዋጋ ትሰ​ጠኝ?” አለው። ጦቢ​ትም፥ “አንተ ወን​ድሜ ዘመ​ድ​ህ​ንና ስም​ህን ዐውቅ ዘንድ እወ​ዳ​ለሁ” አለው።

12 እር​ሱም፥ “እኔስ የወ​ን​ድ​ምህ የታ​ላቁ አና​ንያ ዘመድ አዛ​ርያ ነኝ” አለው።

13 ጦቢ​ትም አለው፥ “አንተ ወን​ድሜ ደኅና ነህን? ወገ​ን​ህ​ንና ሀገ​ር​ህን ዐውቅ ዘንድ መር​ም​ሬ​አ​ለ​ሁና አት​ን​ቀ​ፈኝ፤ ነገር ግን አንተ በእ​ው​ነቱ ከደ​ግና ከተ​ባ​ረከ ወገን ነህ፤ እኔም የታ​ላቁ የሴ​ም​ዩን ልጆች አና​ን​ያ​ንና ኢታ​ያ​ንን ዐው​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እን​ሰ​ግድ ዘንድ ከእ​ነ​ርሱ ጋር አብ​ረን ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሄደን ነበር፤ በኵ​ራ​ቱ​ንና የእ​ህ​ላ​ች​ንን ዐሥ​ራት ወስ​ደን ነበር፤ ነገር ግን በአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን በደል አል​በ​ደ​ል​ንም።

14 ወን​ድሜ አንተ ግን ከደግ ቤተ ሰብ ነህ፤ ነገር ግን ንገ​ረኝ፤ ደመ​ወ​ዝ​ህን ምን እን​ስ​ጥህ? በየ​ቀኑ አንድ ድራ​ህማ እን​ስ​ጥ​ህን? ምግ​ብ​ህስ ከልጄ ጋር ይሁን?

15 በደ​ኅና ከተ​መ​ለ​ሳ​ችሁ በደ​መ​ወ​ዝህ ላይ እጨ​ም​ር​ል​ሃ​ለሁ፤” እን​ደ​ዚ​ህም ጨረሱ።

16 ጦብ​ያ​ንም አለው፥ “ትሄዱ ዘንድ፥ ትከ​ና​ወ​ኑም ዘንድ ተዘ​ጋጁ።” ልጁም ለመ​ን​ገድ ስን​ቃ​ቸ​ውን አዘ​ጋጀ፤ አባ​ቱም አለው፥ “ከዚህ ሰው ጋር ሂድ፤ በሰ​ማ​ያት የሚ​ኖር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ገ​ዳ​ች​ሁን ያቅ​ና​ላ​ችሁ፤ መል​አ​ኩም አብ​ሮ​አ​ችሁ ይሂድ፤” ሁለ​ቱም ወጥ​ተው ሄዱ፤ ሌላው ልጃ​ቸ​ውም ተከ​ተ​ላ​ቸው።

17 እናቱ ሐናም አለ​ቀ​ሰች፤ ጦቢ​ት​ንም እን​ዲህ አለ​ችው፥ “ልጄን ለምን ላክ​ኸው? እርሱ በፊ​ታ​ችን የሚ​ወ​ጣና የሚ​ገባ፥ በእ​ጃ​ችን ያለ ምር​ኩ​ዛ​ችን አይ​ደ​ለ​ምን?

18 ብሩስ ይጥፋ የል​ጄም ቤዛ ይሁን!

19 የም​ን​ኖ​ር​በት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሰ​ጠን ይበ​ቃ​ና​ልና።”

20 ጦቢ​ትም አላት፥ “እኅቴ አት​ጨ​ነቂ፤ በደ​ኅና ይመ​ለ​ሳል፤ በዐ​ይ​ኖ​ች​ሽም ታይ​ዋ​ለሽ።

21 ቸር መል​አክ በፊቱ ይሄ​ዳ​ልና፥ ጎዳ​ና​ው​ንም ያቃ​ና​ለ​ታ​ልና፥ በደ​ኅ​ናም ይመ​ለ​ሳ​ልና።”

22 ሐናም ልቅ​ሶ​ዋን ተወች።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች