ስለዚህ ልጆቼ ከምጽዋት ምን እንደ ሚገኝና ክፋት ወዴት እንደሚመራ አይታችሁአል፥ ሞትን ያመጣል፤ አሁን ግን ትንፋሽ አጠረኝ።” በአልጋው አስተኙት፤ ሞተ፥ በክብርም ተቀበረ።
“አሁንም ልጄ፥ ምጽዋት የምታደርገውን እይ፤ ከሞት ታድናለች፤ ታጸድቃለችም።” ጦቢትም ይህን ተናግሮ ሞተ፤ ባልጋው ላይ ሳለም ነፍሱ ከሥጋው ተለየች። መቶ አምሳ ስምንት ዐመትም ሆኖት ነበር። በክብርም ቀበሩት፤