መጽሐፈ ጦቢት 12:6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ሩፋኤልም ያንጊዜ ሁለቱን ሁሉ ጠራቸው፤ ገለል አድርጎም እንዲህ አላቸው፥ “እግዚአብሔርን አመስግኑት፤ ለእርሱም ተገዙ፤ ለስሙም ምስጋና አቅርቡ፤ ስላደረገላችሁም በጎ ነገር ሁሉ በሰው ሁሉ ፊት እመኑበት፤ እግዚአብሔርን አመስግኑት፤ ስሙንም አመስግኑ፤ የእግዚአብሔርንም ሥራ በክብር ተናገሩ፤ ተአምራቱንም ግለጡ፤ እርሱንም ከማመስገን ቸል አትበሉ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በዚያን ጊዜ ሩፋኤል ሁለቱንም ለብቻቸው ገለል አደረገና እንዲህ አላቸው፦ “እግዚአብሔርን ባርኩ፥ ያደረገላችሁንም በሕያዋን ሁሉ ፊት ምስጋናውን አውሩ፥ ስሙንም ባርኩ፥ አመስግኑም። የእግዚአብሔርን ሥራ ለሰዎች ሁሉ በሚገባ አስታወቁ፥ እሱን ከማመስገን ቸል አትበሉ። |