Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


1 ነገሥት 20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የና​ቡቴ በግፍ መገ​ደል
(በዕብ. ምዕ. 21 ነው።)

1 ለኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊው ለና​ቡቴ በሰ​ማ​ርያ ንጉሥ በአ​ክ​ዓብ ቤት አጠ​ገብ የወ​ይን ቦታ ነበ​ረው።

2 አክ​ዓ​ብም ናቡ​ቴን፥ “በቤቴ አቅ​ራ​ቢያ ነውና የአ​ት​ክ​ልት ቦታ አደ​ር​ገው ዘንድ የወ​ይን ቦታ​ህን ስጠኝ፤ ስለ እር​ሱም ከእ​ርሱ የተ​ሻለ የወ​ይን ቦታ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ፤ ወይም ብት​ወ​ድድ ዋጋ​ውን ወርቅ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ” ብሎ ተና​ገ​ረው።

3 ናቡ​ቴም አክ​ዓ​ብን፥ “የአ​ባ​ቶቼን ርስት እሰ​ጥህ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አያ​ም​ጣ​ብኝ” አለው።

4 አክ​ዓ​ብም አዝኖ ሄደ፤ በአ​ል​ጋ​ውም ላይ ተኝቶ ፊቱን ተሸ​ፋ​ፈነ፤ እን​ጀ​ራ​ንም አል​በ​ላም።

5 ሚስ​ቱም ኤል​ዛ​ቤል ወደ እርሱ ገብታ፥ “ምን ያሳ​ዝ​ን​ሃል? እን​ጀ​ራስ የማ​ት​በላ ምን ሆነ​ሃል?” አለ​ችው።

6 እር​ሱም፥ “ኢይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊ​ውን ናቡ​ቴን፦ የወ​ይ​ን​ህን ቦታ በገ​ን​ዘብ ስጠኝ፤ ወይም ብት​ወ​ድድ በፋ​ን​ታው ሌላ የወ​ይን ቦታ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ ብዬ ተና​ገ​ር​ሁት፤ እርሱ ግን የአ​ባ​ቶ​ቼን ርስት አል​ሰ​ጥ​ህም ስለ አለኝ ነው” አላት።

7 ሚስቱ ኤል​ዛ​ቤ​ልም፥ “አሁ​ንም አንተ የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ሆነህ እን​ደ​ዚህ ታደ​ር​ጋ​ለ​ህን? ተነሣ፤ እን​ጀ​ራ​ንም ብላ፤ ራስ​ህ​ንም አጽና፤ ልብ​ህም ደስ ይበ​ላት፤ የኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊ​ው​ንም የና​ቡ​ቴን የወ​ይን ቦታ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ” አለ​ችው።

8 በአ​ክ​ዓ​ብም ስም ደብ​ዳቤ ጻፈች፤ በማ​ኅ​ተ​ሙም አተ​መ​ችው፤ በከ​ተ​ማው ወደ ነበ​ሩ​ትና ከና​ቡ​ቴም ጋር ወደ ተቀ​መ​ጡት ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችና አለ​ቆች ደብ​ዳ​ቤ​ውን ላከች።

9 የዚ​ያች ደብ​ዳ​ቤም ቃል እን​ዲህ ይላል፥ “ጾምን ጹሙ፤ ናቡ​ቴ​ንም በሕ​ዝቡ መካ​ከል በከ​ፍ​ተኛ ቦታ አስ​ቀ​ም​ጡት፤

10 ሁለት የሐ​ሰት ምስ​ክ​ሮ​ች​ንም በፊቱ አስ​ቀ​ም​ጡና፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንና ንጉ​ሡን ሰድ​ቦ​አል ብለው ይመ​ስ​ክ​ሩ​በት፤ አው​ጥ​ታ​ች​ሁም እስ​ኪ​ሞት ድረስ በድ​ን​ጋይ መት​ታ​ችሁ ግደ​ሉት።”

11 በከ​ተ​ማ​ውም የተ​ቀ​መ​ጡት የከ​ተ​ማው ሰዎ​ችና ሽማ​ግ​ሌ​ዎች፥ አለ​ቆ​ችም ኤል​ዛ​ቤል እን​ዳ​ዘ​ዘ​ቻ​ቸ​ውና ወደ እነ​ርሱ በተ​ላ​ከው ደብ​ዳቤ እንደ ተጻ​ፈው እን​ዲሁ አደ​ረጉ።

12 የጾም አዋ​ጅም ነገሩ፤ ናቡ​ቴ​ንም በሕ​ዝቡ ፊት በከ​ፍ​ተኛ ቦታ አስ​ቀ​መ​ጡት።

13 ሁለ​ቱም የዐ​መፅ ልጆች የሆኑ ሰዎች ገብ​ተው በፊቱ ቆሙ፤ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንና ንጉ​ሡን ሰድ​በ​ሃል” ብለው መሰ​ከ​ሩ​በት። የዚያ ጊዜም ከከ​ተማ አው​ጥ​ተው በድ​ን​ጋይ ደብ​ድ​በው ገደ​ሉት።

14 ወደ ኤል​ዛ​ቤ​ልም፥ “ናቡቴ በድ​ን​ጋይ ተደ​ብ​ድቦ ሞተ” ብለው ላኩ።

15 ኤል​ዛ​ቤ​ልም በሰ​ማች ጊዜ አክ​ዓ​ብን፥ “ናቡቴ ሞቶ​አል እንጂ በሕ​ይ​ወት አይ​ደ​ለ​ምና በገ​ን​ዘብ ይሰ​ጥህ ዘንድ እንቢ ያለ​ውን የኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊ​ውን የና​ቡ​ቴን የወ​ይን ቦታ ተነ​ሥ​ተህ ውረስ” አለ​ችው።

16 አክ​ዓ​ብም ኢይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊው ናቡቴ እንደ ሞተ በሰማ ጊዜ ወደ ኢይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊው ወደ ናቡቴ ወይን ቦታ ሊወ​ር​ሰው ተነ​ሥቶ ወረደ።

17 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቴስ​ብ​ያ​ዊው ኤል​ያ​ስን እን​ዲህ አለው፦

18 “ተነ​ሥ​ተህ በሰ​ማ​ርያ የሚ​ኖ​ረ​ውን የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ንጉሥ አክ​ዓ​ብን ትገ​ናኝ ዘንድ ውረድ፤ እነሆ፥ ይወ​ር​ሰው ዘንድ በወ​ረ​ደ​በት በና​ቡቴ የወ​ይን ቦታ ውስጥ አለ።

19 እን​ዲ​ህም ብለህ ንገ​ረው፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ናቡ​ቴን ገድ​ለህ ወረ​ስ​ኸው፤ ስለ​ዚ​ህም ደግሞ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ጅቦ​ችና ውሾች የና​ቡ​ቴን ደም በላ​ሱ​በት ስፍራ የአ​ን​ተን ደም ደግሞ ውሾች ይል​ሱ​ታል፤ አመ​ን​ዝ​ራ​ዎ​ችም በደ​ምህ ይታ​ጠ​ባሉ” ብለህ ንገ​ረው።

20 አክ​ዓ​ብም ኤል​ያ​ስን፥ “ጠላቴ ሆይ! አገ​ኘ​ኸ​ኝን?” አለው። እር​ሱም እን​ዲህ ብሎ መለ​ሰ​ለት፥ “አግ​ኝ​ቼ​ሃ​ለሁ፤ ታስ​ቈ​ጣው ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉ አድ​ር​ገ​ሃ​ልና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦

21 እነሆ፥ ክፉ ነገር አመ​ጣ​ብ​ሃ​ለሁ፤ እሳ​ትን ከኋ​ላህ አነ​ድ​ዳ​ለሁ፤ ዐጥር ተጠ​ግቶ እስ​ከ​ሚ​ሸን ድረስ የአ​ክ​ዓ​ብን ዘር አጠ​ፋ​ዋ​ለሁ፤ በእ​ስ​ራ​ኤል ውስጥ ያሉ​ት​ንም፥ የሌ​ሉ​ት​ንም እነ​ቅ​ላ​ለሁ፤

22 በሥ​ራ​ህም አስ​ቈ​ጥ​ተ​ኸ​ኛ​ልና፥ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም አስ​ተ​ሃ​ልና ቤት​ህን እንደ ናባጥ ልጅ እንደ ኢዮ​ር​ብ​ዓም ቤት እንደ አኪ​ያም ልጅ እንደ ባኦስ ቤት አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ።”

23 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ ብሎ ተና​ገረ፥ “በኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤል ቅጥር አጠ​ገብ ኤል​ዛ​ቤ​ልን ውሾች ይበ​ሉ​አ​ታል፥

24 ከአ​ክ​ዓ​ብም ወገን በከ​ተ​ማ​ዪቱ ውስጥ የሞ​ተ​ውን ውሾች ይበ​ሉ​ታል፤ በሜ​ዳ​ውም የሞ​ተ​ውን የሰ​ማይ ወፎች ይበ​ሉ​ታል።”

25 ነገር ግን አክ​ዓብ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉን ያደ​ርግ ዘንድ ራሱን ሸጠ፤ ሚስቱ ኤል​ዛ​ቤል አስ​ታ​ዋ​ለ​ችና።

26 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ፊት ያጠ​ፋ​ቸው አሞ​ራ​ው​ያን እንደ ሠሩት ሁሉ፥ ጣዖ​ትን በመ​ከ​ተል እጅግ ርኩስ ነገ​ርን ሠራ።

27 አክ​ዓ​ብም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት የተ​ነሣ ደነ​ገጠ፤ ልብ​ሱ​ንም ቀደደ፤ እያ​ለ​ቀ​ሰም ሄደ፤ በሰ​ው​ነ​ቱም ላይ ማቅ ለበሰ፤ ጾመም፤ ኢይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊው ናቡ​ቴ​ንም በገ​ደ​ለ​በት ቀን ደግሞ ማቅ ለብሶ ነበር።

28 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ስለ አክዓብ ወደ ባሪ​ያው ወደ ኤል​ያስ መጣ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለው፦

29 “አክ​ዓብ በፊቴ እንደ ደነ​ገጠ አየ​ህን? በፊቴ በልጁ ዘመን በቤቱ ላይ ክፉ ነገር አመ​ጣ​ለሁ እንጂ በእ​ርሱ ዘመን ክፉ ነገር አላ​መ​ጣም።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos