Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ኢዮብ 24:13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

13 “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን እነ​ዚ​ህን ለምን አል​ገ​ሠ​ጻ​ቸ​ውም? በም​ድር ላይ ሳሉ አላ​ስ​ተ​ዋ​ሉም፥ የቅ​ን​ነት መን​ገ​ድ​ንም አላ​ዩም። በአ​ደ​ባ​ባ​ይ​ዋም አል​ሄ​ዱም።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

13 “በብርሃን ላይ የሚያምፁ፣ ጐዳናውን የማያውቁ፣ በመንገዱም የማይጸኑ አሉ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

13 “እነዚህ በብርሃን ላይ የሚያምፁ ናቸው፥ መንገዱን አያውቁም፥ በጎዳናውም አይጸኑም።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

13 “ብርሃንን የሚጠሉ ሰዎች አሉ፤ ብርሃንም ምን እንደ ሆነ ስለማያውቁ የብርሃንን መንገድ አይከተሉም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

13 እነዚህ በብርሃን ላይ የሚያምፁ ናቸው፥ መንገዱን አያውቁም፥ በጎዳናውም አይጸኑም።

Ver Capítulo Copiar




ኢዮብ 24:13
26 Referencias Cruzadas  

እር​ስ​ዋም በእ​ኩለ ሌሊት ተነ​ሥታ፥ እኔ አገ​ል​ጋ​ይህ ተኝቼ ሳለሁ፥ ልጄን ከብ​ብቴ ወሰ​ደች፤ በብ​ብ​ቷም አስ​ተ​ኛ​ችው፤ የሞ​ተ​ው​ንም ልጅ​ዋን በእኔ ብብት አስ​ተ​ኛ​ችው።


ድሆ​ችን ከከ​ተ​ማ​ውና ከገዛ ቤቶ​ቻ​ቸው አባ​ረ​ሩ​አ​ቸው የሕ​ፃ​ና​ት​ንም ነፍስ እጅግ አስ​ጮሁ፤


ሥራ​ቸ​ው​ንም ዐውቆ ለጨ​ለማ ዳረ​ጋ​ቸው። በሌ​ሊ​ትም እንደ ሌባ ናቸው።


በጨ​ለማ ቤቶ​ችን ይነ​ድ​ላል፤ በቀን ይሸ​ሸ​ጋሉ፤ ብር​ሃ​ን​ንም አያ​ዩም።


የም​ድ​ርን ዳርቻ ይይዝ ዘንድ፥ ከእ​ር​ስ​ዋም ኃጥ​ኣ​ንን ያና​ውጥ ዘንድ።


የኃ​ጥ​ኣ​ንን ብር​ሃ​ና​ቸ​ውን ከል​ክ​ለ​ሃ​ልን? የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞ​ች​ንስ ክንድ ሰብ​ረ​ሃ​ልን?


በቀን ጨለማ ያገ​ኛ​ቸ​ዋል፥ በቀ​ት​ርም ጊዜ በሌ​ሊት እን​ዳሉ ይር​መ​ሰ​መ​ሳሉ።


የኃጥኣን መንገዶች ግን ጨለማ ናቸው። እንዴት እንደሚሰናከሉም አያውቁም።


ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “ ገና ለጥ​ቂት ጊዜ ብር​ሃን ከእ​ና​ንተ ጋር ነው፤ በጨ​ለማ የሚ​መ​ላ​ለስ የሚ​ሄ​ድ​በ​ትን አያ​ው​ቅ​ምና ጨለማ እን​ዳ​ያ​ገ​ኛ​ችሁ ብር​ሃን ሳለ​ላ​ችሁ ተመ​ላ​ለሱ፤


“በዐ​ይ​ና​ቸው አይ​ተው፥ በል​ባ​ቸ​ውም አስ​ተ​ው​ለው እን​ዳ​ይ​መ​ለ​ሱና እን​ዳ​ል​ፈ​ው​ሳ​ቸው ዐይ​ኖ​ቻ​ቸው ታወሩ፤ ልባ​ቸ​ውም ደነ​ደነ።”


በእኔ የማ​ይ​ኖር ቢኖር እንደ ደረቅ ቅር​ን​ጫፍ ወደ ውጭ ይጥ​ሉ​ታል፤ ሰብ​ስ​በ​ውም በእ​ሳት ያቃ​ጥ​ሉ​ታል።


ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም ያመ​ኑ​በ​ትን አይ​ሁድ እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “እና​ን​ተም በቃሌ ጸን​ታ​ችሁ ብት​ኖሩ በእ​ው​ነት ደቀ መዛ​ሙ​ርቴ ናችሁ።


እና​ን​ተስ ከአ​ባ​ታ​ችሁ ከሰ​ይ​ጣን ናችሁ፤ የአ​ባ​ታ​ች​ሁ​ንም ፈቃድ ልታ​ደ​ርጉ ትወ​ዳ​ላ​ችሁ፤ እርሱ ከጥ​ንት ጀምሮ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ በእ​ው​ነ​ትም አይ​ቆ​ምም፤ በእ​ርሱ ዘንድ እው​ነት የለ​ምና፤ ሐሰ​ት​ንም በሚ​ና​ገ​ር​በት ጊዜ ከራሱ አን​ቅቶ ይና​ገ​ራል፤ ሐሰ​ተኛ ነውና፤ የሐ​ሰ​ትም አባት ነውና።


ይህን እን​ዲህ ላደ​ረገ ሞት እን​ደ​ሚ​ገ​ባው እነ​ርሱ ራሳ​ቸው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍርድ እያ​ወቁ፥ እነ​ርሱ ብቻ የሚ​ያ​ደ​ር​ጉት አይ​ደ​ለም፤ ነገር ግን ሌላ​ውን ያነ​ሣ​ሡ​ታል፤ ያሠ​ሩ​ታ​ልም።


እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኀጢአት ነው።


ከእኛ ዘንድ ወጡ፥ ዳሩ ግን ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገንስ ቢሆኑ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር፤ ነገር ግን ሁሉ ከእኛ ወገን እንዳልሆኑ ይገለጡ ዘንድ ወጡ።


መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos