Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ኢሳይያስ 21:15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

15 እን​ጀራ ይዛ​ችሁ ከሰ​ልፍ ከሸሹ ከብዙ ሰዎ​ችና በጦር ከጠፉ ከብዙ ሰዎች፥ ፍላጻ ከያዙ ከብዙ ሰዎ​ችና ጦር ከያዙ ከብዙ ሰዎች፥ ቀስ​ቶ​ቻ​ቸው ከተ​ሳ​ቡና በሰ​ልፍ ከወ​ደቁ ከብዙ ሰዎች ያመ​ለ​ጡ​ትን ተቀ​በ​ሏ​ቸው።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

15 ከሰይፍ፣ ከተመዘዘ ሰይፍ፣ ከተደገነ ቀስት፣ ከተፋፋመ ጦርነት ሸሽተዋልና።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

15 ከሰይፍ፥ ከተመዘዘው ሰይፍ፥ ከተለጠጠውም ቀስት ከጽኑም ሰልፍ ሸሽተዋልና።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

15 ሕዝቡ ሁሉ ከሚገደሉበት ሰይፍ፥ ከተደገነባቸው ቀስትና ከጦርነት አደጋ ሁሉ ለማምለጥ በመሸሽ ላይ ናቸው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

15 ከሰይፍ፥ ከተመዘዘው ሰይፍ፥ ከተለጠጠውም ቀስት ከጽኑም ሰልፍ ሸሽተዋልና።

Ver Capítulo Copiar




ኢሳይያስ 21:15
7 Referencias Cruzadas  

የተ​ረ​ፉ​ትም ሁሉ እንደ ተባ​ረረ ሚዳቋ፥ እንደ ባዘነ በግም ይሆ​ናሉ። የሚ​ሰ​በ​ስ​ባ​ቸ​ውም የለም፤ እን​ዲ​ሁም ሰው ሁሉ ወደ ወገኑ ይመ​ለ​ሳል፤ ሁሉም ሰው ወደ ሀገሩ ይሸ​ሻል።


የተ​በ​ተ​ኑት ሁሉ ይሞ​ታሉ፤ የተ​ሰ​በ​ሰ​ቡ​ትም ሁሉ በጦር ይወ​ድ​ቃሉ።


ብዙ​ዎች አሕ​ዛብ እንደ ብዙ ውኃ ናቸው፤ ከፏ​ፏቴ ውስጥ በኀ​ይል እን​ደ​ሚ​ወ​ርድ እንደ ብዙ ውኃ ፈሳሽ ይጮ​ኻሉ፤ ያጠ​ፉ​ታ​ልም፤ እነ​ር​ሱም ከሩቅ ይወ​ር​ዳሉ፤ በተ​ራ​ራም ላይ እን​ዳለ እብቅ፥ በነ​ፋስ ፊት ዐውሎ ነፋስ እን​ደ​ሚ​ያ​ዞ​ረው እንደ መን​ኰ​ራ​ኵር ትቢ​ያም ይበ​ተ​ናሉ።


ነገር ግን አለ​ቆ​ችሽ ሁሉ በአ​ን​ድ​ነት ሸሹ፤ የተ​ማ​ረ​ኩ​ት​ንም በእ​ግር ብረት አሠ​ቃ​ዩ​አ​ቸው፤ ኀይ​ለ​ኞ​ች​ሽም ርቀው ሸሹ።


አሦ​ርም ይወ​ድ​ቃል፤ የሚ​ወ​ድ​ቀ​ውም በሰው ሰይፍ አይ​ደ​ለም፤ የም​ት​በ​ላ​ቸ​ውም የሰው ሰይፍ አይ​ደ​ለ​ችም፤ የሚ​ሸ​ሹም ከሰ​ይፍ ፊት አይ​ደ​ለም ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ቸው ግን ይሸ​ነ​ፋሉ።


ከቃ​ልህ ግርማ የተ​ነሣ አሕ​ዛብ ፈር​ተው ሸሹ፤ አሕ​ዛ​ብም ተበ​ተኑ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos