32 እርሱ የሚያልፍበት መንገድ ያበራል፤ የባሕሩንም ውሃ ወደ ዐረፋ ይለውጠዋል።
32 ያለፈበትን መንገድ ብሩህ ያደርጋል፤ ቀላዩንም ሽበት ያወጣ ያስመስለዋል።
ለምድር ብርሃን ለመስጠት በሰማይ ጠፈር ላይ ሆነው ያብሩ” እንዲሁም ሆነ።
በዚያን ጊዜ ምድር ቅርጽ የሌላትና ባዶ ነበረች፤ ጨለማም በጥልቁ (ውቅያኖስ) ላይ ነበር፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውሃው ላይ ይሰፍ ነበር።
አንተ ግን ብዙ ዘመን ኖረህ በሰላም ትሞታለህ፤ በሰላምም ትቀበራለህ።
በዚህም ዐይነት አብርሃም በቂ ዕድሜ አግኝቶ ካረጀ በኋላ ሞተ፤
ያዕቆብም “ምንም ቢሆን ከእናንተ ጋር አይሄድም፤ ወንድሙ ሞቶአል፤ የቀረው እርሱ ብቻ ነው፤ በመንገድ አንድ ጒዳት ቢደርስበት በእርጅናዬ ዘመን በመሪር ሐዘን ወደ መቃብር እንድወርድ ታደርጉኛላችሁ” አላቸው።
‘ውቅያኖስ በእኔ ውስጥ የለችም’ ይላል፤ ‘ባሕሩም ከእኔ ጋር አይደለችም’ ይላል።
“ወደ ባሕሩ ጥልቀት ወርደሃልን? በውቅያኖስ ወለል ላይ ተመላልሰህ ታውቃለህን?
ውርጩ ውሃን እንደ ድንጋይ ያጠጥራል፤ የባሕሩም ወለል እንደ በረዶ እንዲረጋ ያደርገዋል።
ባሕርን እንደ ፈላ ውሃ ያፍለቀልቀዋል፤ በማሰሮ ውስጥ እንደሚፈላ ዘይትም ያንተከትከዋል።
እርሱ ፍርሀት የማያውቅ ፍጡር ስለ ሆነ፥ በዓለም ላይ እርሱን የሚመስል ፍጡር ከቶ የለም።
ሽበት የክብር ዘውድ ነው። የሚገኘውም በተቀደሰ አኗኗር ነው።
የወጣቶች መመኪያ ብርታታቸው ነው፤ የሽማግሌዎችም መከበሪያ ሽበታቸው ነው።