ዘኍል 7:30 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በአራተኛውም ቀን የሮቤል ልጆች አለቃ የሴድዮር ልጅ ኤሊሱር መባውን አቀረበ፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም በአራተኛው ቀን የሮቤል ሕዝብ አለቃ የስዲዮር ልጅ ኤሊሱር ስጦታውን አመጣ፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በአራተኛውም ቀን የሮቤል ልጆች አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር አቀረበ፤ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም በአራተኛው ቀን መባውን ያቀረበው ከሮቤል ነገድ የሰድዩር ልጅ ኤልጹር ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በአራተኛውም ቀን የሮቤል ልጆች አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር፤ |
ለደኅንነትም መሥዋዕት ሁለት ጊደሮች፥ አምስት አውራ በጎች፥ አምስት አውራ ፍየሎች፥ አምስት የአንድ ዓመት እንስት የበግ ጠቦቶች ነበረ፤ የኬሎን ልጅ የኤልያብ መባ ይህ ነበረ።
መባውም ለእህል ቍርባን በዘይት የተለወሰ መልካም ዱቄት የተሞሉ፥ ሚዛኑ እንደ መቅደሱ ሰቅል ሚዛን መቶ ሠላሳ ሰቅል የሆነ አንድ የብር ወጭት፥ ሚዛኑም ሰባ ስቅል የሆነ አንድ የብር ድስት፤