ከሶርያውያንም ጋር ወደ ሰልፍ በወጣ ጊዜ ከእስራኤል ምድር ታናሽ ብላቴና ሴት ማረከ፤ ለሚስቱም አገልጋይ አደረጋት።
መሳፍንት 9:34 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) አቤሜሌክና ከእርሱም ጋር ያሉት ሕዝብ ሁሉ በሌሊት መጡ። ሰቂማንም በአራት ወገን ከበቡአት። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ስለዚህ አቢሜሌክና ሰዎቹ በሙሉ በሌሊት ወጡ፤ በአራት ምድብ ሆነውም በሴኬም አጠገብ አደፈጡ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ስለዚህ አቤሜሌክና ሰዎቹ በሙሉ በሌሊት ወጡ፤ በአራት ምድብ ሆነውም በሴኬም አጠገብ አደፈጡ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ስለዚህ አቤሜሌክና ተከታዮቹ ሁሉ በሌሊት ተነሥተው ከሴኬም ውጪ በአራት ወገን ተከፍለው ደፈጣ አደረጉ፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) አቤሜሌክና ከእርሱም ጋር ያሉት ሕዝብ ሁሉ በሌሊት ተነሡ፥ በሴኬምም አቅራቢያ በአራት ወገን ሸመቁበት። |
ከሶርያውያንም ጋር ወደ ሰልፍ በወጣ ጊዜ ከእስራኤል ምድር ታናሽ ብላቴና ሴት ማረከ፤ ለሚስቱም አገልጋይ አደረጋት።
ነገም ፀሐይ በወጣች ጊዜ ማልደህ ተነሣ፤ ከተማዪቱንም ክበባት፤ እነሆም፥ እርሱና ከእርሱ ጋር ያሉት ሕዝብ በአንተ ላይ በወጡ ጊዜ እጅህ እንዳገኘች አድርግበት።”
በነጋም ጊዜ የአቤድ ልጅ ገዓል ወጥቶ በከተማዪቱ መግቢያ በር ቆመ፤ አቤሜሌክና ከእርሱ ጋር ያሉት ሕዝብም ከሸመቁበት ስፍራ ተነሡ።