La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




መሳፍንት 18:8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እነ​ዚ​ያም አም​ስቱ ሰዎች ወደ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ወደ ሶራ​ሕና ወደ እስ​ታ​ሔል ተመ​ለሱ፤ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ው​ንም፥ “ምን አስ​ቀ​ም​ጦ​አ​ች​ኋል?” አሉ​አ​ቸው።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ወደ ጾርዓና ወደ ኤሽታኦል እንደ ተመለሱ ወገኖቻቸው፣ “የሄዳችሁበት ጕዳይ እንዴት ሆነ?” በማለት ጠየቋቸው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ወደ ጾርዓና ወደ ኤሽታኦል እንደተመለሱ ወገኖቻቸው፥ “የሄዳችሁበት ጉዳይ እንዴት ሆነ?” በማለት ጠየቋቸው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

አምስቱም ሰዎች ወደ ጾርዓና ወደ ኤሽታኦል በተመለሱ ጊዜ ወገኖቻቸው፦ “ምን ወሬ አላችሁ?” ብለው ጠየቁአቸው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ወደ ወንድሞቻቸውም ወደ ጾርዓና ወደ ኤሽታኦል ተመለሱ፥ ወንድሞቻቸውም፦ ምን ወሬ ይዛችኋል? አሉአቸው።

Ver Capítulo



መሳፍንት 18:8
7 Referencias Cruzadas  

በቆ​ላው፥ አስ​ጣል፥ ሳራዓ፥ አሳ፤


ከዳን ወገን የሆነ ማኑሄ የሚ​ባል አንድ የሶ​ራሕ ሰው ነበረ፤ ሚስ​ቱም መካን ነበ​ረች፤ ልጅም አል​ወ​ለ​ደ​ችም ነበር።


ወን​ድ​ሞ​ቹም፥ የአ​ባቱ ቤተ ሰቦ​ችም ሁሉ ወረዱ፤ ይዘ​ውም አመ​ጡት፤ በሶ​ሬ​ሕና በኢ​ስ​ታ​ሔል መካ​ከል ባለው በአ​ባቱ በማ​ኑሄ መቃ​ብር ቀበ​ሩት። እር​ሱም እስ​ራ​ኤ​ልን ሃያ ዓመት ገዛ​ቸው።


ከዳን ወገ​ንም የጦር ዕቃ የታ​ጠቁ ስድ​ስት መቶ ሰዎች ከዚያ ከሶ​ራ​ሕና ከእ​ስ​ታ​ሔል ተነ​ሥ​ተው ሄዱ።


የዳ​ንም ልጆች ከወ​ገ​ና​ቸው አም​ስት ጽኑ​ዓን ሰዎች ምድ​ሪ​ቱን እን​ዲ​ሰ​ል​ሉና እን​ዲ​መ​ረ​ምሩ፥ “ሂዱ ምድ​ሪ​ቱ​ንም ሰልሉ” ብለው ከሶ​ራ​ሕና ከኢ​ስ​ታ​ሔል ላኩ። እነ​ዚ​ያም ወደ ተራ​ራ​ማዉ ወደ ኤፍ​ሬም ሀገር ወደ ሚካ ቤት መጥ​ተው በዚያ አደሩ።


አም​ስ​ቱም ሰዎች ሄዱ፤ ወደ ሌሳም ደረሱ፤ በው​ስ​ጡም የነ​በ​ሩ​ትን ሕዝብ ተዘ​ል​ለው አዩ​አ​ቸው፤ እንደ ሲዶ​ና​ው​ያ​ንም ልማድ ጸጥ ብለው፥ ዐር​ፈው፥ ተዘ​ል​ለ​ውም ተቀ​ም​ጠው ነበር፤ በተ​መ​ዘ​ገ​በች የር​ስ​ታ​ቸው ምድ​ርም ቃልን መና​ገር አል​ቻ​ሉም፤ ከሲ​ዶ​ና​ው​ያ​ንም ርቀው ይኖሩ ነበር። ከሶ​ር​ያ​ው​ያ​ንም ጋር ግን​ኙ​ነት አል​ነ​በ​ራ​ቸ​ውም።


እነ​ር​ሱም፥ “ምድ​ሪቱ እጅግ መል​ካም እንደ ሆነች አይ​ተ​ናል፤ ተነሡ፤ በእ​ነ​ርሱ ላይ እን​ውጣ፤ እና​ንተ ዝም ትላ​ላ​ች​ሁን? ትሄዱ ዘንድ፥ ምድ​ሪ​ቱ​ንም ለመ​ው​ረስ ትገቡ ዘንድ ቸል አት​በሉ።