ዘፀአት 38:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በአዜብ በኩል የመጋረጃዎች ርዝመት ዐሥራ አምስት ክንድ፥ ምሰሶዎቹም ሦስት፥ እግሮቹም ሦስት ነበሩ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ከሦስት ምሰሶዎችና ከሦስት መቆሚያዎች ጋራ ርዝመታቸው ዐሥራ ዐምስት ክንድ የሆኑ መጋረጃዎች በአንድ በኩል ባለው መግቢያ ላይ ነበሩ፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በአንድ በኩል የመጋረጃዎቹ ርዝመት ዐሥራ አምስት ክንድ ነበረ፥ ሦስት ምሰሶዎች እና ሦስት እግሮች ነበሩ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም በአንድ በኩል ያለው የበሩ መጋረጃ ስድስት ሜትር ከስድሳ ሳንቲ ሜትር ተኩል ርዝመት፥ ሦስት ምሰሶዎችና ሦስት እግሮችም ነበሩት። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በአንድ ወገንም የመጋረጆቹ ርዝመት አሥራ አምስት ክንድ፥ ምሰሶቹም ሦስት፥ እግሮቹም ሦስት ነበሩ። |
እንዲሁም በሁለተኛው ወገን በአደባባዩ ደጅ በዚህና በዚያ ዐሥራ አምስት ክንድ ርዝመት ያላቸው መጋረጃዎች፥ ሦስትም ምሰሶዎች፥ ሦስትም እግሮች ነበሩ።