በምዕራብም ወገን አምሳ ክንድ ርዝመት ያላቸውን መጋረጃዎች፥ ዐሥሩንም ምሰሶዎች፥ ዐሥሩንም የናስ እግሮች፥ ለምሰሶዎቹም የብር ኵላቦችንና ዘንጎችን አደረገ።
ዘፀአት 38:13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በምሥራቅም ወገን አምሳ ክንድ ርዝመት ያላቸውን መጋረጃዎችን አደረገ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም በፀሓይ መውጫ በኩል ያለው የምሥራቁም ጫፍ ወርዱ ዐምሳ ክንድ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በምሥራቅም በኩል አምሳ ክንድ ርዝመት ያላቸው መጋረጃዎች ነበሩ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የመግቢያው ደጅ ባለበት በምሥራቅ በኩል የአደባባዩ ስፋት ኻያ ሁለት ሜትር ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በምሥራቅም ወገን አምሳ ክንድ ርዝመት ያላቸውን መጋረጆች አደረገ። |
በምዕራብም ወገን አምሳ ክንድ ርዝመት ያላቸውን መጋረጃዎች፥ ዐሥሩንም ምሰሶዎች፥ ዐሥሩንም የናስ እግሮች፥ ለምሰሶዎቹም የብር ኵላቦችንና ዘንጎችን አደረገ።